Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Selam/
Senior Member
Posts: 17038
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: አዲሱ የኦቶማን ኢምፓየር ፤ አቢይ አህመድ የአጼ ልብነ ድንግልን ድክመት እንዳይደግም

Post by Selam/ » 02 Jul 2024, 21:11

እግዜር ይይልህ ፥ ታላቁን አታቱርክን ዘርጥጠህ ወደሚገባው የግራኝ መሃመድ የውኃ ልክ አወረድከው።

Abere wrote:
02 Jul 2024, 14:38
____ I do not think Abiy Ahmed in any form or manner is comparable Atse Lebne-Dengel. The former is anti-Ethiopian both in intent and deed, whereas the latte( Atse Lebne-Dengle) was a true Ethiopian. In other words, we are talking Abiy Ahmed who himself actually is Gragn Amhed. In many cases, Gragn Ahmed was better than Abiy Ahmed.


___ If Turkey single handedly plays the role, then it is obvious Ahmed Gragn is sitting with Amhed Gragn himself. :mrgreen:

Dama
Member+
Posts: 6481
Joined: 22 Jun 2024, 21:05

Re: አዲሱ የኦቶማን ኢምፓየር ፤ አቢይ አህመድ የአጼ ልብነ ድንግልን ድክመት እንዳይደግም

Post by Dama » 02 Jul 2024, 21:31

Selam/ wrote:
02 Jul 2024, 20:07

I approve this message
Dama
<< አስተዳደሩ ቆሻሻ እስከሆነ ድረስ የባህር በር ይመጣል ይሄዳል፤ ባህር ኃይል ይገነባል ይፈርሳል። ያለፉት ውዳቂ መንግስቶች ይኸን ካደረጉ፣ የአንተውስ አጭበርባሪ ዓብዮት ሸጦህና ለውጦህ እንደማይሰደድ ምን ማስተማመኛ አለህ?

Horus
Senior Member+
Posts: 40300
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አዲሱ የኦቶማን ኢምፓየር ፤ አቢይ አህመድ የአጼ ልብነ ድንግልን ድክመት እንዳይደግም

Post by Horus » 02 Jul 2024, 21:42

ሲሊማ ኢትዮጵያ! ኤረክላሙ አሁንም አለ !


Odie
Member+
Posts: 6277
Joined: 24 Jun 2024, 23:07

Re: አዲሱ የኦቶማን ኢምፓየር ፤ አቢይ አህመድ የአጼ ልብነ ድንግልን ድክመት እንዳይደግም

Post by Odie » 02 Jul 2024, 23:55

አይ ሆረስ!
ይህ ምልከታህ አብይ አህመድ ግራኝ ኢትዮዽያዊ መሪ ቢሆን ኖሮ ጊዜ ስጥቶ እንደውጭ ፖሊስ ሃሳብ ማስላስል ይቻል ነበር:: አገርና ህዝብ ያሉበት ውድቀት እያወቅክ ህዝቡ ፎከስ ካረገበት ነገር ጊዜ የሚያባክን የሚያበሳጭ ነገር ትለጥፋለህ:: ተደማጭህ ማን ንው? የብልፅግና ካድሬ? አብይ? ለሹመት አይጠይቁህም? ወይስ ስልጣን ስጥተውሃል? አብይ ኢትዮዽያ አትፈርስም ብሎ ቃል ገብቶልሃል? ምክንያቱም ኢትዮዽያ ያለች ይመስል ስለኢትዮዽያ ትመስጣለህ:: ኢትዮዽያ የምትባል አገር ከትግሬ የጦር አበጋዞችና የዘር ፋሽስቶች የኦሮም ይዘር ፋሽስቶች ተቀብለው እየዘረፉ እየጋጡ ሬፕ እያረጉዋት ነው:: አንተ ደግሞ ስለ አህመድ ግራኝ ኦቶማን ኤምፖየር ትተርካለህ:: Don’t you see the elephant in the room in Arat kilo. አህመድ ግራኝማ አራት ኪሎ ተቀምጧል እርምህን አውጣ ወይ ስለሱ ሞግት!!

Odie
Member+
Posts: 6277
Joined: 24 Jun 2024, 23:07

Re: አዲሱ የኦቶማን ኢምፓየር ፤ አቢይ አህመድ የአጼ ልብነ ድንግልን ድክመት እንዳይደግም

Post by Odie » 02 Jul 2024, 23:59

Horus wrote:
02 Jul 2024, 13:39
የዛሬይቱ ኢትዮጵያ የ1520ዎቹ አገራችን አይደለችም። 17 አመታት በፈጀው የኦቶማን ኢምፓየር ፕሮክሲ የግራኝ ወረራ ግራኝ የተሸነፈው በመጀመሪያው የባደቄ (የሞጆ) ወንዝ ጦርነት ብቻ ነው። ያሸነፉትም ቀስተኞቹ አመያዎች ናቸው ። ከዚያ በኋላ የብርቱካን (የፖርቹጋል) ክርስቲያን ጦር እርዳታ እስከ መጣ ድረስ ግራኝ ቤተ ክርስቲያን እና በጻሕፍቷን አቃጥሎ ለ1000 አመታት ያከማቸችውን የወርቅ መስቀሎች ከመላ ኢትዮጵያ ለ17 አመት ዘረፈ ። ታሪክ በውል እንደ ዘገበው ልብነ ድንግል እጅግ ደካማ ንጉስ ነበር።

ዛሬ ቱርክ በተመሳሳይ በመላ አፍሪካ ተስፋፍታ አዲሱን ኦቶማን ኢምፓየር ለመገምባት አምርራ እየሰራች ነው ። ባፍሪካ ውስጥ ሱማሊያ የተባልቸው ፍርስራሽ አገር የቱርክ ቅኝ ግዛት ነች ቢባል ማጋነን አይሆንም ። ቱርክ የፖለቲካ ጥቅም የላትም ። የቱርክ አላማ ሃብትና ሃብት ብቻ ነው ። ይህን ለማሳካት የምትጠቀመው ደሞ ፖለቲካ ወይም ዲፕሎማሲ አይደለም፣ የጦር ኃይል ነው ።

አሁን ላይ ባፍሪካ ቀንድ ተፋጠው ያሉት የአረብ ኤምሬቶች ባንድ በኩልና ቱርክና ቀጥር በሌላ በኩል ነው። ቱርክ የሶማሊያን ወደቦች ይዛ የኢትዮጵያን ንግድ መቆጣጠር ነው አላማዋ። ኢምሬት የበርበራ ወደብ ይዘው ከወዲሁ 30% የኢትዮጵያ ንግድ ተቆጣጥረዋል ። ኢምሬት ኢትዮጵያ በነሱ ላይ ጥገኛ እንድትሆን ነው የሚፈልጉት ። ቱርክ በነሱ ላይ ጥገኛ እንድንሆን ነው የሚፈልጉት ።

በእኔ እምነት ኢትዮጵያ የባህር ኃይል እንዳይኖራት ከሚፈልጉት አገሮች ቁጥር አንዷ ቱርክ ነች ። አቢይም ሆነ አጽቀ ስላሴ በምንም አይነት ቱርክን ማመን፣ የቱርክን ምክር መስማት የለባቸውም።

ሶማሌላንድ በውድም ሆነ በግድ ፤ በኢትዮጵያ ታወቀችም አልታወቀች ነጻ አገር መሆኑዋ ሳይታለም የተፈታ ነው ። ዞሮ ዞሮ ቱርክም ከሱማሌላንድ ሬፑብሊክ ጋር ውል ፈጥራ የነሱን ባህር ለመቆጣጠር መሥራቷ አይቀሬ ነው ። ስለዚህ የኢትዮጵያ ፍኖተ ተግባር መሆን ያለበት የሚከተለው ነው ።

እሺ ካሉ ከቱርክ ጋር የባህር ኃይላችንን በመገንባቱ ፓርትነር ሆነው የሶማሌላንንም ነጻነት እንዲደግፉ ማድረግ ። ይህ ለ4ቱም አገሮች ሶማሊያ፣ ሶማሌላ አገር፣ ኢትዮጵያና ቱርክ ዊን ዊን ፖሊሲ ነው ። በዚህ የማይመቻት አረብ ኢሚሬት ቢሆንም ኢሚሬት ወታደራዊ ኃይል የላቸውም ፤ እንዲያም ከቱርክ ጋርም ያላቸው ዝምድና በጣም እያደገ ስለሆነ የኢምሬት ትቅምም ማስገባት ይቻላል።

ይህ ካልሆነና አቢይና አጽቀ ስላሴ በቱርክ ተታልለው ከሱማሌላንድ ውል ወደ ኋላ ካፈገፈጉ ኢትዮጵያ ወደ ፊት በፍጹም የባህር ኃይል አይኖራትም ፣ ቤዝ አይኖራትም። ሶማሌላንድ የጦር ቤዝ የሰጠችን በአንድና አንድ ጥቅም ብቻ ነው ፤ የአገርነት እውቅና ለማግኘት ።

ስለሆነም ቱርኮች ኤም ኦ ዩውን እንዲዘገይ ፣ እንዲደናቀፍና ፣ እንዲከስም ካደረጉ ሶማሌላንድ አንድም በኢትዮጵያ ያላት እምነት ያከትማል ፤ ሌላም አዲስ አገር እውቅና ከሰጣት በኋላ በፍጹም የጦር ቤዝ ለኢትዮጵያ አትሰጥም ! ስለዚህ እነአጽቀ ስላሴ ከፍተኛ በቱርክ የመታለል አደጋ ላይ ይገኛሉ።

ይልቁንም ኢትዮጵያ በጀመረችው ድፍረት ቀጥላበት የሶማሌላንድ ውልን ባስቸኳይ መፈረምና ከዚያ በኋላ የዲፕሎማሲ ጨዋታ ማጧጧፍ ነው ያለባት ። ለምን ቢባል ...

ነገ ኢትዮጵያ በሉዋያ ጦር ሰፈር ብታቆም ቱርክ የመታደር ኃይል አምጥቶ መላ ሱማሌን የመጠበቅ አላማም ፍላጎትም የለውም ። ዞሮ ዞሮ ከአል ሻባብና አይሲስ ጋር የማያባራ ጦርነት ውስጥ እንደ ሚገባ ስለሚያውቅና ደሞም ከኢትዮጵያ ጋር ተቆራርጦ ባፍሪካም ያለውን ተጽኖ ማጣት ስለማይፈልግ ቱርክ በጭራሽ የራሱን ቬትናም ባፍሪካ ቀንድ እንዲኖረው አይፈልግም ። የቱርክ ፍላጎት ገንዘብ ነው።፣

የኢትዮጵያ እድል ግን አሁን ክሪቲካል ነጥብ ላይ ይገኛል።

(ስለ ታይፕ ግድፈት ይቅርታ)
አይ ሆረስ!
ይህ ምልከታህ አብይ አህመድ ግራኝ ኢትዮዽያዊ መሪ ቢሆን ኖሮ ጊዜ ስጥቶ እንደውጭ ፖሊስ ሃሳብ ማስላስል ይቻል ነበር:: አገርና ህዝብ ያሉበት ውድቀት እያወቅክ ህዝቡ ፎከስ ካረገበት ነገር ጊዜ የሚያባክን የሚያበሳጭ ነገር ትለጥፋለህ:: ተደማጭህ ማን ንው? የብልፅግና ካድሬ? አብይ? ለሹመት አይጠይቁህም? ወይስ ስልጣን ስጥተውሃል? አብይ ኢትዮዽያ አትፈርስም ብሎ ቃል ገብቶልሃል? ምክንያቱም ኢትዮዽያ ያለች ይመስል ስለኢትዮዽያ ትመስጣለህ:: ኢትዮዽያ የምትባል አገር ከትግሬ የጦር አበጋዞችና የዘር ፋሽስቶች የኦሮም ይዘር ፋሽስቶች ተቀብለው እየዘረፉ እየጋጡ ሬፕ እያረጉዋት ነው:: አንተ ደግሞ ስለ አህመድ ግራኝ ኦቶማን ኤምፖየር ትተርካለህ:: Don’t you see the elephant in the room in Arat kilo. አህመድ ግራኝማ አራት ኪሎ ተቀምጧል እርምህን አውጣ ወይ ስለሱ ሞግት!!

Horus
Senior Member+
Posts: 40300
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አዲሱ የኦቶማን ኢምፓየር ፤ አቢይ አህመድ የአጼ ልብነ ድንግልን ድክመት እንዳይደግም

Post by Horus » 03 Jul 2024, 00:55

ስልጣን አጠገብ ሳትደርሱ በናንተ አንጎል እንዳስብ ይህን ሁሉ ግዜያችሁን የምታባክኑ ስልጣን አፋፍ ብትደርሱን ምን ማድረግ እንደ ምትሞክሩ አመላካች ነው። አትልፉ ሆረስ የራሱን ሓሳብ የሚያስብበት የራሱ አንጎል አለው ! :idea: :idea: :idea:

Selam/
Senior Member
Posts: 17038
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: አዲሱ የኦቶማን ኢምፓየር ፤ አቢይ አህመድ የአጼ ልብነ ድንግልን ድክመት እንዳይደግም

Post by Selam/ » 03 Jul 2024, 07:27

ምንም ስሜት የማይሰጥ ብሽቅ ዓርፍተ ነገር ነው። ሰው ውዳቂ የሚሆነው በጎረቤቱ አንጎል ማሰብ ሲጀምር ሳይሆን፣ ከጎረቤቱ መማር ሳይችልና እኔ ብቻ አዋቂ ነኝ ሲል ነው።

If I may use my favorite Scotts’ expression for NPDs, you are full of ‘ne’er-do-well!’

Horus wrote:
03 Jul 2024, 00:55
ሆረስ የራሱን ሓሳብ የሚያስብበት የራሱ አንጎል አለው !

Abere
Senior Member
Posts: 14874
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: አዲሱ የኦቶማን ኢምፓየር ፤ አቢይ አህመድ የአጼ ልብነ ድንግልን ድክመት እንዳይደግም

Post by Abere » 03 Jul 2024, 10:16

ሆረስ፥

አብይ አህመድ በታጠቀው መሳሪያ እና በእጁ በያዘው ብዕር (fraud authority) የአገርን ዕጣ ሊጎዳ ወይም ሊጠቅም እንደሚችል እሙን ነው - ስልጣኔ ብሎ ከተቀመጠባት ባርጩማ እስከሚነሳ።

ቁም ነገሩ የሰውየው ብስለት እና የራዕይ ጥራት ላይ ነው። አንድ መሳሪያ ህጻን ልጅ ላይ ከገባ አደጋ ያደርሳል - ወይም አንድ አእምሮ ንክ ከያዘው መሳሪያው ብዙ ፍጅት ያደርሳል። አብይ አህመድ እስከ አሁን ኢትዮጵያን በሰከነ አእምሮ እየመራ ሳይሆን እየገደላት ያለሰው ነው።

ይህ ሰው የኢትዮጵያ ህዝብ በወደብ ጉዳይ ያለውን የማይሞት ጥያቄ በሚገባ ያውቃል - ማንም ተራ ዜጋ እንደሚያውቀው ሁሉ። ኢትዮጵያ የተፈጥሮ የባህር በር አያስፈልጋትም የሚል አንዳች ዜጋ አይኖርም ከወያኔ በስተቀር። ታዲያ ለዚች ክፉ የጭንቅ እና ጦርነት ሰዐት ብዙ እረጭ እረጭ አበዛ። ለምን ቀጥታ አሰብን አይጠይቅም? :mrgreen: የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ህዝብ ዘላቂ ጥያቄ በሰላም ይሁን በጦርነት የሚደመደም ጉዳይ ነው። ይህ አጭበርባሪ ግን ያለወቅቱ የጠየቀበት ምክንያት ከልቡ አይደለም - ችግሩን ለማስተንፈስ ነው። ባዶ እረጭ እረጭ ነው።

እኔ አህመድ ግራኝን ለማንሳት የፈለግሁት። ቀዳማዊ አህመድ ግራኝ እንድሁ በቱርክ የተጋዘ እንደሆነ ሁሉ ዳግማዊ ግራኝ አህመድ ( ግራኝ አብይ አህመድ) እንድሁ የቱርክ የቤት ስራ ይቀበላል ነው። በአብይ አህመድ እንጎል ያለችው ኦሮምያ እንጅ ኢትዮጵያ አይደለችም። እነ ሌንጮ እና ወዘተ አማካሪዎቹ ኢትዮጵያን አፍርሰን ኦሮምያ የምትመስል አገር ነው የምንሰራው ነው ብለው የነገሩን። ታዲያ በቀዳማዊ ግራኝ አህመድ የተፈጠረው አገር የማጥፋት በማግስቱ የሞጋሳ መስፋፋት አሁን በዳግማዊ ግራኝ አህመድ እየተደረገ አይደለም እንደ አይን ባወጣ መልኩ? I say it again, Abiy Ahmed is not a legitimate person to sign any historical treaties.
Horus wrote:
02 Jul 2024, 16:47
አበረ፣
ጉ'ዳዩ አቢይን መውደድ ወይም መጥላት አይደለም ። ዛሬ ላይ አገሪቱን ወክሎ አለም አቀፍ ውል የሚፈራረመው እሱ ነው ። ለማንኛውም ለምን የግራኝና አጸ ልብነ ድንግልን እንዳነሳሁ ለማየት ካሻህ ክቡር ተክለ ጻዲቅ መኩሪያ በ1966 (ኢ፣ካ) ያሳተሙትን 840 ገጽ 'የግራኝ አህመድ ወረራ' የተሰኘው ታሪከ ድጓቸን ተመልከት። ለምን ደካማ ንጉስ እንዳሉት ማየት ትችላለህ ።



Post Reply