-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
ጉራማይሌው ቢቀር
ከውጭ ያለውን ኢትዮጵያዊ ጉራማይሌ ንግግር እንድያቆም ትመክራላችሁ ተብሎ ሲጠበቅ ጭራሹኑ እናንተ አገር ውስጥ ያላችሁት ተዘፈቃችሁበት ምነው?! ኧረ ተው! ባይሆን የውጩን ቋንቋ መጠቀም ካለባችሁ ሙሉውን ያንን ቋንቋ ተጠቀሙ::
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ጉራማይሌው ቢቀር
ዓይኔን ሰው አማረው፤
የሰው ያለህ የሰው!
አያ ብር አለንጋው የሌጌዎን መሪ፣
ልጅ፤ እስከ ማእዜኑ ያስማንዲዮስ መሪ፤
አያ ደሙ በኔ የሳጥናኤል መሪ፣
የቀበሮ እንግዳ በቤቱ አሣዳሪ፣
ተበግ ተቀበሮ ቀበሮን አክባሪ፣
ቀበሮን ወደ ቤት በግን ገደል መሪ፣
የበግ ለምድ ለበሶ በጐችን አባራሪ፣
በቀበሮው አዋጅ አገሩን ወራሪ፣
በለሰለሰ እርሻ አሜኬላ ዘሪ፣
እጅግ ተጠንቅቆ አባቱን አፍቃሪ፣
አባቱን አፍቅሮ እናት አቃጣሪ፣
እናቱን አቃጥሮ አባት አሣሣሪ፣
አባት አሣሥሮ በናቱ መካሪ፣
በናቱ ላይ መክሮ አዋጅ አስነጋሪ፣
በግራ የቆመው ሲመለስ ወደ ቀኝ፣
እኔም በናታችሁ ጐዳናው ሳይርቀኝ፣
በዚያን ጊዜ እናንተን የሚያይ ሰው ናፈቀኝ።
ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ
የሰው ያለህ የሰው!
አያ ብር አለንጋው የሌጌዎን መሪ፣
ልጅ፤ እስከ ማእዜኑ ያስማንዲዮስ መሪ፤
አያ ደሙ በኔ የሳጥናኤል መሪ፣
የቀበሮ እንግዳ በቤቱ አሣዳሪ፣
ተበግ ተቀበሮ ቀበሮን አክባሪ፣
ቀበሮን ወደ ቤት በግን ገደል መሪ፣
የበግ ለምድ ለበሶ በጐችን አባራሪ፣
በቀበሮው አዋጅ አገሩን ወራሪ፣
በለሰለሰ እርሻ አሜኬላ ዘሪ፣
እጅግ ተጠንቅቆ አባቱን አፍቃሪ፣
አባቱን አፍቅሮ እናት አቃጣሪ፣
እናቱን አቃጥሮ አባት አሣሣሪ፣
አባት አሣሥሮ በናቱ መካሪ፣
በናቱ ላይ መክሮ አዋጅ አስነጋሪ፣
በግራ የቆመው ሲመለስ ወደ ቀኝ፣
እኔም በናታችሁ ጐዳናው ሳይርቀኝ፣
በዚያን ጊዜ እናንተን የሚያይ ሰው ናፈቀኝ።
ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ጉራማይሌው ቢቀር
ጥንተ ሀገሬ ሆይ ጥንተ ተደንግሎ፤
ሕጻናቱ ታርደው ያንቺም ልብ ቆስሎ፤
ሕዝቡ ተሰደደ አንቺን ተከትሎ፤
የሕጻናቱን ደም አዘክሪ ኵሎ፡፡
አስጨነቀኝ ስደትሽ፤
እመቤቴ ተመለሽ፡፡
ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ
ሕጻናቱ ታርደው ያንቺም ልብ ቆስሎ፤
ሕዝቡ ተሰደደ አንቺን ተከትሎ፤
የሕጻናቱን ደም አዘክሪ ኵሎ፡፡
አስጨነቀኝ ስደትሽ፤
እመቤቴ ተመለሽ፡፡
ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ጉራማይሌው ቢቀር
ተቀምጬ
ተቀምጬ፣
የሐዘን የትካዜ ሙዚቃ ስሰማ፣
ጓደኛዬ ሁኖ የሲጋራው ጢስ፣
ጢሱ ቅታሬውን እየጎንጎን ክራሴ በላይ፣
የብቻ መሆኔ አዳኛ ሲሳይ፣
ጢሱና ሙዚቃው እየተባበረ፣
የስሜቴን ስሜት የልቤን የውስጡን እየበረበረ፣
ሲያወጣው ፈልቅቆ፣
እኔን እኔነቴን፣ ራሴን ከውስጡ፣ ከውስጤ ሰልቆ፣
ፈርፍሮ፣
ፈልፍሎ፣
ፈታ ፈታታና፣
ደም - ብረት፣ ሐሞት - መርዝ ሊያናግረው ሲል፣
ድንገት ድምጽ ሰማሁ፣
አንዲቱ መዝጊዬ ሰማሁ ስትንኳኳ፣
ገብቶ የነበረው ልቤን ሊያመሰኳ፣
የሙዚቃው ስልቱ፣ የጢሱ ውበቱ በደንገት ቀጥ አለ፣
የበሬም መንኳኳት በዚያው ልክ ቀጠለ፡፡
ዮሃንስ አድማሱ
ተቀምጬ፣
የሐዘን የትካዜ ሙዚቃ ስሰማ፣
ጓደኛዬ ሁኖ የሲጋራው ጢስ፣
ጢሱ ቅታሬውን እየጎንጎን ክራሴ በላይ፣
የብቻ መሆኔ አዳኛ ሲሳይ፣
ጢሱና ሙዚቃው እየተባበረ፣
የስሜቴን ስሜት የልቤን የውስጡን እየበረበረ፣
ሲያወጣው ፈልቅቆ፣
እኔን እኔነቴን፣ ራሴን ከውስጡ፣ ከውስጤ ሰልቆ፣
ፈርፍሮ፣
ፈልፍሎ፣
ፈታ ፈታታና፣
ደም - ብረት፣ ሐሞት - መርዝ ሊያናግረው ሲል፣
ድንገት ድምጽ ሰማሁ፣
አንዲቱ መዝጊዬ ሰማሁ ስትንኳኳ፣
ገብቶ የነበረው ልቤን ሊያመሰኳ፣
የሙዚቃው ስልቱ፣ የጢሱ ውበቱ በደንገት ቀጥ አለ፣
የበሬም መንኳኳት በዚያው ልክ ቀጠለ፡፡
ዮሃንስ አድማሱ
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ጉራማይሌው ቢቀር
ጎበና እና አሉላ
አጥንቱን ልልቀመው መቃብር ቆፍሬ ፤
ጎበናን ተሸዋ አሉላን ተትግሬ፤
ስመኝ አድሬያለሁ ትላንትና ዛሬ፤
ጎበናን ለአሞራ አሉላን ለጭሬ፡
ተሰባሰቡና ተማማሉ ማላ ፤
ጎበና ከሸዋ ተትግሬም አሉላ
ጎበና ሴት ልጁን ሊያስተምር ፈረስ
አሉላ ሴት ልጁን ጥይት ሊያስተኩስ
አገሬ ተባብራ ካልረገጠች እርካብ
ነገራችን ሁሉ የእምቧይ ካብ የእምቧይ ካብ።
ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ
አጥንቱን ልልቀመው መቃብር ቆፍሬ ፤
ጎበናን ተሸዋ አሉላን ተትግሬ፤
ስመኝ አድሬያለሁ ትላንትና ዛሬ፤
ጎበናን ለአሞራ አሉላን ለጭሬ፡
ተሰባሰቡና ተማማሉ ማላ ፤
ጎበና ከሸዋ ተትግሬም አሉላ
ጎበና ሴት ልጁን ሊያስተምር ፈረስ
አሉላ ሴት ልጁን ጥይት ሊያስተኩስ
አገሬ ተባብራ ካልረገጠች እርካብ
ነገራችን ሁሉ የእምቧይ ካብ የእምቧይ ካብ።
ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ
Re: ጉራማይሌው ቢቀር
ወይ ካላካበቱ ወይም ካላምታቱ
ማን ለማ ይሰጣል ከዚያ ከሱረቱ
መንግስቱ ለማ
እስረኞቹ ግጥሞቼ
ማን ለማ ይሰጣል ከዚያ ከሱረቱ
መንግስቱ ለማ
እስረኞቹ ግጥሞቼ
Last edited by Horus on 16 Jul 2023, 01:12, edited 1 time in total.
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ጉራማይሌው ቢቀር
እገበያ መሀል ፈስ እያንዛረጡ
አውራ ጎዳና ላይ ዳቦ እየገመጡ
ቤተክስያን ገብቶ ትምባሆ እየጠጡ
እንዲህ ነው ወይ ጣሊያን አልጋ ላይ ሲወጡ?
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ
አውራ ጎዳና ላይ ዳቦ እየገመጡ
ቤተክስያን ገብቶ ትምባሆ እየጠጡ
እንዲህ ነው ወይ ጣሊያን አልጋ ላይ ሲወጡ?
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ጉራማይሌው ቢቀር
በሳህን ሲሆ ነው የሚያምረው ወጥህ
ድንች አትላክልኝ ከመሬት ነቅለህ
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ
ድንች አትላክልኝ ከመሬት ነቅለህ
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ
Re: ጉራማይሌው ቢቀር
Revelations,
እነዚህን ሁለት ነገሮች ስለ መንግስቱ ለማ ታውቅ ኖሮዋልን?
አንድ፣ ጣሊያን ተባሮ የሃይለ ስላሴ መንግስት እንደ ገና ሲደራጅ ማጆሪቲው የዙፋን መኳንንቶች የኢትዮጵያ አንደኛ ብሄራዊ ቋንቋ እንግሊዝኛ እንዲሆን ሲከራከሩ መንግስቱ ለማ ገና ሁለተኛ ደረጃ ሳይጨርስ ዙፋን ቀርቦ አማርኛ ቋንቋ እንዴት የማንነታችን መገለጫ እንደ ሆነ ኃይለ ስላሴን ያሳመነ ምሁር መሆኑን!!!
የዚህ ድንቅ ሊቅ አባት የታወቁ አለቃ ባለቅኔ ሲሆኑ እናታቸው ጉራጌ እንደ ሆኑ! ልክ የታላቁ ምኒልክ ትህትና ከጉራጌ እናቱ እንደ ወረሰ ሁሉ መንግስቱ ለማም ትሁትነትና ሚዛናዊነት የወረሰው ከጉራጌ እናቱ ነበር!!
እነዚህን ሁለት ነገሮች ስለ መንግስቱ ለማ ታውቅ ኖሮዋልን?
አንድ፣ ጣሊያን ተባሮ የሃይለ ስላሴ መንግስት እንደ ገና ሲደራጅ ማጆሪቲው የዙፋን መኳንንቶች የኢትዮጵያ አንደኛ ብሄራዊ ቋንቋ እንግሊዝኛ እንዲሆን ሲከራከሩ መንግስቱ ለማ ገና ሁለተኛ ደረጃ ሳይጨርስ ዙፋን ቀርቦ አማርኛ ቋንቋ እንዴት የማንነታችን መገለጫ እንደ ሆነ ኃይለ ስላሴን ያሳመነ ምሁር መሆኑን!!!
የዚህ ድንቅ ሊቅ አባት የታወቁ አለቃ ባለቅኔ ሲሆኑ እናታቸው ጉራጌ እንደ ሆኑ! ልክ የታላቁ ምኒልክ ትህትና ከጉራጌ እናቱ እንደ ወረሰ ሁሉ መንግስቱ ለማም ትሁትነትና ሚዛናዊነት የወረሰው ከጉራጌ እናቱ ነበር!!