Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Meleket
- Member
- Posts: 4954
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » 03 Mar 2026, 05:00
እኛ ኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በሰው ልጆች መካከል ፍቅር እንጂ፡ ጥላቻና ተንኮል እንዲያንሰራፋ ፍላጎታችን አይደለም።
የአማራ ህዝብና የትግራይ ህዝብ ለዘመናት በፍቅር የኖሩና የተጋመዱ ክቡር ወንድማማች ህዝቦች ናቸው። በእልህና በጥላቻ በሚመሩ በአንዳንድ ‘ፖለቲከኞች’ የስህተት ቀመር ምክንያት፡ እነዚህ ወንድማማች ህዝቦች ሳይወዱ በግድ እንዲናቆሩ ብዙ ተንኮል ተሸርቧል። እኛ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች ግን በዚህ ችግር መሃል እሳት ማቀጣጠል ሳይሆን፡ እንደ መልካም ጎረቤት መጠን መፍትሄ እናጋራለን።
'ትግማራ' - 'የአማራና ትግራይ አወዛጋቢ ስፍራዎች' ሰላማዊ የመፍትሄ አማራጭ ቁልፍ ሃሳብ
1.) አማራና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ እያነሱ ሲናቆሩባቸው የቆዩ ስፍራዎች፡ ጽንፈኛ አስተሳሰብ ያላቸውን አስተዳዳሪዎችንና ሃላፊዎችን በሙሉ በቀጠናው ሃይሎች ትብብር አማካኝነት መቀዬር።
2.) በነዚህ አወዛጋቢ ስፍራዎች በሃላፊነት የሚቀመጡ አካላት በአባት ወይም በእናት ከአማራና ከትግራይ የሚወለዱ እንዲሆኑ አድርጎ ማዋቀር።
3.) “ሙሉ አማራ ነኝ”፣ “ሙሉ ትግሬ ነኝ” ብሎ በዘረኝነት ቆፈን የሚጋጋጥ ዜጋ፡ አንድም አወዛጋቢ ባልሆነው የክልሉ ክፍል ሆኖ መኖር፡ አሊያም አዲስ በሚመደቡት ከሁለቱ ግዙፋን ብሄሮች ወላጆች የተወለዱ ከጽንፈኛና ዘረኛ አስተሳሰብ በጸዱ የትግማራ አካላት ስር እንዲስተዳደር ማድረግ።
4.) በነዚህ አካባቢ የሚዋቀሩ የጸጥታ አካላት ሙሉ በሙሉ፡ የአማራና የትግራይ ክልል ውስጥ ባሉ የጸጥታ አካላት ሙሉ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ማድረግ።
5.) ከጎረቤት ሃገር ከሱዳን ሆነ ከኤርትራ የጸጥታ ሃይሎች ጋር በዚህ ረገድ ሙሉ ትብብር ማድረግ።
6.) ነውጠኛ ጽንፈኛ አስተሳሰብ ያላቸውን አካላት አስፈላጊውን ገንቢ ትምህርት እንዲቀስሙ በማድረግ አንድም ትጥቅ ማስፈታት አሊያም ለአዲሱ የትግማራ አመራር ታዛዥነታቸውን በማረጋገጥ በበጎ የልማትና የጸጥታ ስራ ማሰማራት።
7.) የአማራ ሆነ የትግራይ ‘ከውዝግብ’ ነጻ የሆኑ ክፍሎች፡ የወንጀለኞች መደበቂያ እንዳይሆኑ፡ የትግማራ አመራር ለሚተገብራቸው ስራ ሙሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ ማስቻል።
8.) የአማርኛና የትግርኛ ቋንቋዎች በነዚህ ስፍራዎች ህጋዊነታቸው ተረጋግጦ፡ ሁሉም የመንግሥት ጽሕፈት ቤቶች ያለ አንዳች አድልዎ እነዚህን ቋንቋዎች እንዲጠቀም ማድረግ። ትምህርትም በሁለቱ ቋንቋዎች እንዲሰጥ ማድረግ።
9.) ተንኮል ለመዝራት ጥላቻ ለማስፋፋት የሚጥሩ የውጭ ሆነ የውስጥ ሃይሎችን በተናበበ መልኩ መመከት። የአወዛጋቢ ስፍራዎች ህዝቦች፡ ችግር ሊያባብስ የሚችለውን ተንኮልና ሴራ ያነገበውን የብልጽግና ‘ሪፈረንደም’ ሆነ አላስፈላጊ ቁርቁስ ውስጥ የሚያስገባ፡ ግዜና ወቅት ያልጠበቀውን መለያዬትን የሚያበረታታውን ‘ምርጫን’ ገሸሽ እንዲሉ አድርጎ፡ ለሰላምና ለወንድማማችነት ለሚተጋው ለትግማራ አመራር ድጋፋቸውን እንዲለግሱ ብርቱ ጥረት ማድረግ።
10.) የትግማራ አመራሮች ሁሌም በአማራ እና በትግራይ ክልል ካሉ አመራሮች ሆነ ኃይሎች ጋር የሚመካከሩበትንና፡ የልማት ሆነ የጸጥታ ግስጋሲያቸውን የሚያሳዩበት ግንኙነቶችን ያለማቋረጥ በአመት ቢያንስ 4 ግዜ በየሶስት ወራት መከወን።
ለግዜው በኛ በኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች ነጻ እይታ፡ የአማራና የትግራይ አወዛጋቢ ስፍራዎች ግዚያዊ ክስተት በዚህ መልኩ ሊቀረፍ እንደሚችል እንገምታለን። እስቲ ጎበዝ የሚጨመረውን ጨምራችሁ የሚጎድለውን አጉድላችሁ ወደ ትግባሬ አምሩ። ለዚህ ሰላማዊና ቅዱስ መፍትሄ የኤርትራ ህዝብና መንግሥት ሁሌም ከአማራና ከትግራይ ህዝቦች ጎን በመሆን የበኩሉን በጎ አስተዋጽኦ ለማድረግ ወደኋላ እንደማይል ስንገልጥላችሁ ደግሞ፡ የክልሎቹ ህዝቦች ለሚያስፈልጋቸውን የሸቀጥ የንግድ እና የመሰረተ ልማት ቁሶች፡ ኤርትራ ምጽዋን ሆነ አሰብን ክፍት በማድረግ ለቀጠናው ሰላም፡ ለነዚህ ክቡር ወንድም ህዝቦች መፋቀር የራሷን ገንቢ ሚናና አሻራ ለማሳረፍ ቆርጣ እንደተነሳችም ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
ተጻፈ ለትግማራ ትግባሬ፡ በአሳማራና አዶማራ ይሁንታ፡ በኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በተለመደው ኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር።
እንጉታ፦
viewtopic.php?f=2&t=376412
viewtopic.php?f=2&t=376410&p=1610930#p1610930
viewtopic.php?f=2&t=376410
-
Meleket
- Member
- Posts: 4954
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » 03 Mar 2026, 09:09
ወዳጃችን Axumezana እላይ ባስቀመጥነው የ ‘ትግማራ’ – ‘የአማራና ትግራይ አወዛጋቢ ስፍራዎች’ ሰላማዊ የመፍትሄ አማራጭ ቁልፍ ሃሳብ ዙርያ ምልከታው ምን እንደሚመስል ቢያካፍለን ከታላቅ አክብሮት ጋር ጋብዘነዋል!
Axumezana wrote: ↑02 Mar 2026, 12:20
እውሩ አይተ መለከት!
.... ጉዞ ወደ ቀይ ባህር እየተባለ
ትግራይንና አማራን ለማጣላት ተንኰል ትዘራለህ፤ No demarcation and no ፅምዶ!
የመለከት እይታ ሁሌ ድንግዝግዝ ነው
ማንነቱን ክዶ ማዬት የተሳነው
Colonial syndrome እያሰቃየው
ሲቧጥጥ ይኖራል ጥልያን ባስተማረው
-
Meleket
- Member
- Posts: 4954
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » 05 Mar 2026, 03:10
እነዚህ የተለያየ አመለካከት ያላቸው የቀጠናው የፖለቲካ ኃይሎች ደጋፊዎችና የመረጃ ቤተሰቦች፡ በዚህ ማለትም በአማራና ትግራይ አወዛጋቢ ስፍራዎች ላለው ችግር ምን ዓይነት መፍትሔ ይጠቁማሉ?
እዚህ በተገለጸው የመፍትሔ ሃሳብ ላይስ ምን ዓይነት አስተያዬት አላቸው?
የበኩላቸውን ሁነኛ የመፍትሔ ሃሳብ እንዲያጋሩን፡ እዚህ በክብር ጋብዘናቸዋል!
ተመሳሳይ የመፍትሔ ሃሳብም “በአማራና በኦሮሞ ድንበር አወዛጋቢ ስፍራዎችም ላይ በመጠቀም”፡ ‘የግጭት ስፍራዎችን’ በመላና በጥበብ የትብብርና የፍቅር ስፌት በመስፋት፡ ትብብርና ያጋራ እድገትን ማምጣት አይቻልምን?
ላልሰሙት እያሰማችሁ እስቲ ጎበዝ እንሆ ሜዳው፡ ተወያዩ እስቲ! ለሁላችሁም መልካም መልካሙን ሁሉ እዬተመኘን!
Meleket wrote: ↑03 Mar 2026, 05:00
እኛ ኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በሰው ልጆች መካከል ፍቅር እንጂ፡ ጥላቻና ተንኮል እንዲያንሰራፋ ፍላጎታችን አይደለም።
የአማራ ህዝብና የትግራይ ህዝብ ለዘመናት በፍቅር የኖሩና የተጋመዱ ክቡር ወንድማማች ህዝቦች ናቸው። በእልህና በጥላቻ በሚመሩ በአንዳንድ ‘ፖለቲከኞች’ የስህተት ቀመር ምክንያት፡ እነዚህ ወንድማማች ህዝቦች ሳይወዱ በግድ እንዲናቆሩ ብዙ ተንኮል ተሸርቧል። እኛ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች ግን በዚህ ችግር መሃል እሳት ማቀጣጠል ሳይሆን፡ እንደ መልካም ጎረቤት መጠን መፍትሄ እናጋራለን።
'ትግማራ' - 'የአማራና ትግራይ አወዛጋቢ ስፍራዎች' ሰላማዊ የመፍትሄ አማራጭ ቁልፍ ሃሳብ
1.) አማራና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ እያነሱ ሲናቆሩባቸው የቆዩ ስፍራዎች፡ ጽንፈኛ አስተሳሰብ ያላቸውን አስተዳዳሪዎችንና ሃላፊዎችን በሙሉ በቀጠናው ሃይሎች ትብብር አማካኝነት መቀዬር።
2.) በነዚህ አወዛጋቢ ስፍራዎች በሃላፊነት የሚቀመጡ አካላት በአባት ወይም በእናት ከአማራና ከትግራይ የሚወለዱ እንዲሆኑ አድርጎ ማዋቀር።
3.) “ሙሉ አማራ ነኝ”፣ “ሙሉ ትግሬ ነኝ” ብሎ በዘረኝነት ቆፈን የሚጋጋጥ ዜጋ፡ አንድም አወዛጋቢ ባልሆነው የክልሉ ክፍል ሆኖ መኖር፡ አሊያም አዲስ በሚመደቡት ከሁለቱ ግዙፋን ብሄሮች ወላጆች የተወለዱ ከጽንፈኛና ዘረኛ አስተሳሰብ በጸዱ የትግማራ አካላት ስር እንዲስተዳደር ማድረግ።
4.) በነዚህ አካባቢ የሚዋቀሩ የጸጥታ አካላት ሙሉ በሙሉ፡ የአማራና የትግራይ ክልል ውስጥ ባሉ የጸጥታ አካላት ሙሉ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ማድረግ።
5.) ከጎረቤት ሃገር ከሱዳን ሆነ ከኤርትራ የጸጥታ ሃይሎች ጋር በዚህ ረገድ ሙሉ ትብብር ማድረግ።
6.) ነውጠኛ ጽንፈኛ አስተሳሰብ ያላቸውን አካላት አስፈላጊውን ገንቢ ትምህርት እንዲቀስሙ በማድረግ አንድም ትጥቅ ማስፈታት አሊያም ለአዲሱ የትግማራ አመራር ታዛዥነታቸውን በማረጋገጥ በበጎ የልማትና የጸጥታ ስራ ማሰማራት።
7.) የአማራ ሆነ የትግራይ ‘ከውዝግብ’ ነጻ የሆኑ ክፍሎች፡ የወንጀለኞች መደበቂያ እንዳይሆኑ፡ የትግማራ አመራር ለሚተገብራቸው ስራ ሙሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ ማስቻል።
8.) የአማርኛና የትግርኛ ቋንቋዎች በነዚህ ስፍራዎች ህጋዊነታቸው ተረጋግጦ፡ ሁሉም የመንግሥት ጽሕፈት ቤቶች ያለ አንዳች አድልዎ እነዚህን ቋንቋዎች እንዲጠቀም ማድረግ። ትምህርትም በሁለቱ ቋንቋዎች እንዲሰጥ ማድረግ።
9.) ተንኮል ለመዝራት ጥላቻ ለማስፋፋት የሚጥሩ የውጭ ሆነ የውስጥ ሃይሎችን በተናበበ መልኩ መመከት። የአወዛጋቢ ስፍራዎች ህዝቦች፡ ችግር ሊያባብስ የሚችለውን ተንኮልና ሴራ ያነገበውን የብልጽግና ‘ሪፈረንደም’ ሆነ አላስፈላጊ ቁርቁስ ውስጥ የሚያስገባ፡ ግዜና ወቅት ያልጠበቀውን መለያዬትን የሚያበረታታውን ‘ምርጫን’ ገሸሽ እንዲሉ አድርጎ፡ ለሰላምና ለወንድማማችነት ለሚተጋው ለትግማራ አመራር ድጋፋቸውን እንዲለግሱ ብርቱ ጥረት ማድረግ።
10.) የትግማራ አመራሮች ሁሌም በአማራ እና በትግራይ ክልል ካሉ አመራሮች ሆነ ኃይሎች ጋር የሚመካከሩበትንና፡ የልማት ሆነ የጸጥታ ግስጋሲያቸውን የሚያሳዩበት ግንኙነቶችን ያለማቋረጥ በአመት ቢያንስ 4 ግዜ በየሶስት ወራት መከወን።
ለግዜው በኛ በኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች ነጻ እይታ፡ የአማራና የትግራይ አወዛጋቢ ስፍራዎች ግዚያዊ ክስተት በዚህ መልኩ ሊቀረፍ እንደሚችል እንገምታለን። እስቲ ጎበዝ የሚጨመረውን ጨምራችሁ የሚጎድለውን አጉድላችሁ ወደ ትግባሬ አምሩ። ለዚህ ሰላማዊና ቅዱስ መፍትሄ የኤርትራ ህዝብና መንግሥት ሁሌም ከአማራና ከትግራይ ህዝቦች ጎን በመሆን የበኩሉን በጎ አስተዋጽኦ ለማድረግ ወደኋላ እንደማይል ስንገልጥላችሁ ደግሞ፡ የክልሎቹ ህዝቦች ለሚያስፈልጋቸውን የሸቀጥ የንግድ እና የመሰረተ ልማት ቁሶች፡ ኤርትራ ምጽዋን ሆነ አሰብን ክፍት በማድረግ ለቀጠናው ሰላም፡ ለነዚህ ክቡር ወንድም ህዝቦች መፋቀር የራሷን ገንቢ ሚናና አሻራ ለማሳረፍ ቆርጣ እንደተነሳችም ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
ተጻፈ ለትግማራ ትግባሬ፡ በአሳማራና አዶማራ ይሁንታ፡ በኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በተለመደው ኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር።
እንጉታ፦
viewtopic.php?f=2&t=376412
viewtopic.php?f=2&t=376410&p=1610930#p1610930
viewtopic.php?f=2&t=376410
Abere wrote: ↑03 Mar 2026, 17:11
...
Selam/ wrote: ↑04 Mar 2026, 10:01
...
Horus wrote: ↑03 Mar 2026, 17:38
...
OPFist wrote: ↑02 Mar 2026, 15:01
...
Misraq wrote: ↑04 Mar 2026, 19:26
...
almaze wrote: ↑04 Mar 2026, 19:40
...
Fed_Up wrote: ↑04 Mar 2026, 22:05
...
Mesob wrote: ↑03 Mar 2026, 16:26
...
-
Meleket
- Member
- Posts: 4954
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » Today, 03:33
የትግራዩ sarcasm እንዲሁም የአማራው Abere በተጨማሪም የብልጥግናው Horus ስለዚህ ጉዳይ ያላቸውን ነጻ አመለካከትና ዘላቂ የመፍትሔ ሃሳብ እንዲያጋሩን፡ በኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር ጋብዘናል እኛ የጎረቤቶቻችንን ሰላምና ልማት የምንሻ ኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች። ዬተለየ ሰላማዊ የመፍትሔ ሃሳብ ካላቸው ያጋሩናል ብለን እንጠብቃለን።
Abere wrote: ↑03 Mar 2026, 17:11
...
Horus wrote: ↑03 Mar 2026, 17:38
...
-
Meleket
- Member
- Posts: 4954
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » Today, 04:06
በቃ ይሄው ነው የመፍትሔ ሃሳብህ ማለት ነውን ወዳጃችን? መልካም መልካሙን ሁሉ ተመኘንልህ።
Axumezana wrote: ↑Today, 03:52
ጅብ በማያውቁት አገር ቆርበት አንጥፉልኝ ይላል!
-
Axumezana
- Senior Member
- Posts: 19003
- Joined: 27 Jan 2020, 23:15
Post
by Axumezana » Today, 05:25
Meleket you have to 1st resolve the problems of your dying Italy made Eritrea.
-
Meleket
- Member
- Posts: 4954
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » Today, 07:43
ወዳጃችን Axumezana ልታናግረን ፈልገህ እንጂ፡ ኤርትራማ ትልቁን ችግሯን አሽቀንጥራ ከጣለች እኮ ቆየች። አሁን፡ ሳትንጠራራ፡ እንደ ዓቕሚቲ እዬኖረች ነው። ይህ ሰላማዊ ኑሮዋ የማይዋጥላቸው አካላት ቢኖሩ አይገርመንም፡ ምክንያቱም እነዚህ አካላትን ነው ከምድረባህሪ መንግለን ያወጣናቸው፡ እኛ የሰው ሃብትን የማንመኘው የኛንም ለማንም አካል አሳልፈን የማንሰጠው፡ ኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች።
ለአወዛጋቢዎቹ የአማራና ትግራይ አዋሳኝ ስፍራዎች፡ ያንተ መፍትሄ “ብሪቶሪያ” ወይም “ህገመንግሥቱ ይከበር” ወይም እንደ ብልጽግኖቹ “ሪፈረንዱም”የሚል ነውን? መቼም አመለካከትህ እንዲያ ከሆነ፡ ከህገመንግስቱ በፊት እንዲሁም ከብሪቶሪያ በኋላ የነበሩትንና ያሉትን ነባራዊ ሁኔታዎች ግምት ውስጥ የሚያስገባ አይመስለንም። እስቲ መፍትሄ ሃሳብ ኣመንጭ፡ እንዲሁ ዙርያ ጥምጥም እየሄድክ ጭራህን ከምትቆላ፡ አይመስልህም?
Axumezana wrote: ↑Today, 05:25
Meleket you have to 1st resolve the problems of your dying Italy made Eritrea.