የብልፅግና እና የ ትህነግ ቱሩፋት!
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወላጋ ዞን ነቀምቴ ውስጥ ሁለት ታዳጊ ልጆችን በቡድን በመሆን የደፈሩ ወጣቶች እስካሁን ድረስ በፖሊስ ቁጥጥር ስር አለመዋላቸውን ፖሊስ እና የአካባቢው ባለሥልጣን ለቢቢሲ ተናገሩ።
የነቀምቴ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮሚሽነር ሻሎ ገለታ ወንጀሉ የተፈጸመው ነቀምቴ ከተማ ውስጥ ባለፈው መስከረም ወር ላይ መሆኑን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።
ነገር ግን ወንጀሉን ከፈጸሙት መካከል “እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ስር የዋለ የለም። ነገር ግን ሁለት ተጠርጣሪዎችን እየፈለግን ነው” ሲሉ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
ሁለቱ ታዳጊ ልጆች በቡድን ሲደፈሩ የሚያሳየው ተንቀሳቃሽ ምሥል ባለፉት ቀናት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት ከተሠራጨ በኋላ በርካቶች ቁጣቸውን እየገለፁ ነው።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cy0gnd81789o
-
Za-Ilmaknun
- Member
- Posts: 4486
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40