Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4486
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

ነቀምቴ እና መቀሌ - የሁለቱ የሴቶች በ ደቦ መደፈሪያ ከተሞች ወግ

Post by Za-Ilmaknun » 01 Nov 2024, 12:21

የብልፅግና እና የ ትህነግ ቱሩፋት!

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወላጋ ዞን ነቀምቴ ውስጥ ሁለት ታዳጊ ልጆችን በቡድን በመሆን የደፈሩ ወጣቶች እስካሁን ድረስ በፖሊስ ቁጥጥር ስር አለመዋላቸውን ፖሊስ እና የአካባቢው ባለሥልጣን ለቢቢሲ ተናገሩ።
የነቀምቴ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮሚሽነር ሻሎ ገለታ ወንጀሉ የተፈጸመው ነቀምቴ ከተማ ውስጥ ባለፈው መስከረም ወር ላይ መሆኑን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።
ነገር ግን ወንጀሉን ከፈጸሙት መካከል “እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ስር የዋለ የለም። ነገር ግን ሁለት ተጠርጣሪዎችን እየፈለግን ነው” ሲሉ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
ሁለቱ ታዳጊ ልጆች በቡድን ሲደፈሩ የሚያሳየው ተንቀሳቃሽ ምሥል ባለፉት ቀናት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት ከተሠራጨ በኋላ በርካቶች ቁጣቸውን እየገለፁ ነው።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cy0gnd81789o