Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Abaymado
Member
Posts: 4404
Joined: 27 Sep 2017, 21:56

በአማራ ክልል የተሰራው ትልቁ የዘይት ፋብሪካ ስራውን ሊጀምር ወራት ይቀሩታል! ይህ ፋብሪካ አብዛኛውን የአገሪቱን የዘይት ፍጆታ ያሟላ ተብሎ ይጠበቃል::

Post by Abaymado » 04 Aug 2019, 11:51


በጎጃም በቡሬ አካባቢ በአማራው ባለ ሀብት አቶ በላይነህ ክንዴ በ 500 ሚልዮን ብር ወጪ የተሰራው የዘይት ፋብሪካ የመጀመርያው ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅዋል::
ከስድስት ወር በኃላ ስራውን እንደሚጀምር ተገልፅዋል::
ይህ ፋብሪካ ሲጠናቀቅ የሃገሪቷን 60 ከመቶ የዘይት ፍላጎት እንደሚሸፍን ተነግሯል :((ምን ያህል እውነት ይሆን?)
ፋብሪካው ባንድ ቀን ወደ 650,000 ሊትር የpalm ዘይት እና 653,332 ሊትር የአኩሪ አተር: የሱፍና የሌሎችን የቅባት እህሎች ዘይት ማምረት ይችላል:: ባጠቃላይ በቀን ከአንድ ሚልዮን በላይ ሊትር ያመርታል ተብሏል:: በተጨማሪ ወደ 120 ሺ ቶን የተቀነባበረ የሰሊጥ ምርት ወደ ውጭ እንደሚልክ ታውቅዋል::
2000 ሰራተኞችንም እንደሚቀጥር ይጠበቃል::
ትልቁ ችግር ግን የመብራት አቅርቦት እንደሆነ ተገልፅዋል!

!

source -amara mass media
Last edited by Abaymado on 04 Aug 2019, 12:23, edited 1 time in total.


Post Reply