Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Naga Tuma
Member+
Posts: 7781
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

ግምታዊ የትንቢት መፈጸም በአራት ቃላት

Post by Naga Tuma » 24 Jul 2026, 19:46

አራቱን ቃላት ያጤንኩኝ ጥቂት ቀናት በፊት ነዉ።

እዚህ መድረክ ላይ ላነበብኩኝ ኣስተያየት መልስ ስሰጥ ለብዙ ዓመታት ያስተዋልኳቸዉ ገጠመኞች ተደማምረዉ ይህን መለኮታዊ ግምት እንዳገኝ ያደረጉ ይመስለኛል።

መለኮታዊ ነገርን በቀላሉ ማንሳት ኣይቻልም። በቀላሉ ማየት ወይም ማለፍ ሃጥዓት ሊሆን ይችላል።

ግምታዊ የትንቢት መፈጸም አራት ቃላት ያልኩኝ ዐለም ሰገድ ማለት እና እግዜር መገለጥ ማለት ናቸዉ።

ምኞት ይሁን መንፈሳዊ ዐለም ሰገድ ማለት የተሰማዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ነበር።

እኔ በዚህ ዘመን እግዜር ተዓምራትን እያሳየ እና እያስቆጠረ ተገልጧል ብዬ የማምን ሰዉ ነኝ።

በጣም የሚደንቀዉ በዚህ ዘመን እግዜር ተዓምራትን እያሳየ መገለጥ ኣንዱ በዐለም ሰገድ ሀረግ በኩል መሆኑ ነዉ።

የዐለም ሕዝብ በሙሉ በዚህ ዘመን በተገለጡት ተዓምራት የምያምኑ ሲሆን የዐለም ሕዝብ ሁሉ ሕዝበ እግዝኣብሔር ይሆናል።

ስለዚህ የእኔ ኣሰላሰል የዐለም ሕዝብን በሙሉ የምያሳምን የእግዜር መገለጥ የዐለም ሰገድን ትንቢት መፈጸም ይሆናል።

Naga Tuma
Member+
Posts: 7781
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ግምታዊ የትንቢት መፈጸም በአራት ቃላት

Post by Naga Tuma » Yesterday, 11:29

ሰገድ፣ ሰገዴ፣ መስገድ፣ መስጊድ መሠረታቸዉ ኣንድ ቃል ነዉ ብሎ መገመት ይቻላል።

ሰገዴ የምያስብል መንፈስ ነዉ። አያን ሰገቺሴ ማለት አያነ ኣሰገደዉ ማለት ነዉ።

የኢትዮጵያ ሃይማኖት መሠረት ይህ ነበረ። በዚህ ስምንተኛዉ ሺህ የተባለ ዘመንም የተገለጠዉ ይሄዉ ነዉ።

አያን ቃሉት ቡኤ ሰገቺሴ ማለት እና እግዝኣብሔር በሰዉ ላይ ኣደረ ማለት ተመሳሳይ ጽንሰሀሳቦች ናቸዉ።

ተጠመቀ የሚባለዉ በዉሃ ነዉ።

እኔ እስከማዉቀዉ ድረስ ዉሃን የምያሰግድ መንፈስ ዬለም።

ይህ ማለት በቀላሉ ሰገደ ማለት እና ተጠመቀ ማለት ምን ማለት ናቸዉ ብሎ መጠየቅ እና የጥንታዊ ኢትዮጵያ የቅዱስ መንፈስ መሠረት ዬትኛዉ ነዉ ብሎ መጠየቅ ያስችላል።

ሰገደ ወይም ሰገዴ ማለት መሠረቱ ኢትዮጵያ ነዉ ብሎ መመለስ ይቻላል።

ተጠመቀ መሠረቱ ከባህር ማዶ ነዉ ብሎ መመለስ ይቻላል።

ሃጥዓቱ መሠረቱ ኢትዮጵያ የነበረ ሰገደ ተወስዶ ተጠመቀ ተብሎ ከባህር ማዶ መጣ።

እኔ ለሰላሳ ኣራት ዓመታት ገደማ ለብቻዬ ኣሰላስዬ፣ ለብቻዬ ኣጥንቼ፣ ለብቻዬ መሠረቱ መስገድ ስለሆነ ኢትዮጵያ የቅዱስ መንፈስ ህዳሴ ብሎም ለዐለም ሁለተኛዉ ሬይነሳንስ ይሆናል እያልኩኝ ነዉ።

Naga Tuma
Member+
Posts: 7781
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ግምታዊ የትንቢት መፈጸም በአራት ቃላት

Post by Naga Tuma » Yesterday, 11:55

ይህ ኣስተያየት ያለዉ ጥልቅ መልዕክት ቅዱስ መንፈስ ኣለ ወይስ ዬለም ይሆናል።

እኔ ቅዱስ መንፈስ ኣለ ብዬ የማምን ብቻ ሳልሆን እየተገለጠልኝ የማይ ነኝ።

ቅዱስ መንፈስ ኣለ ማለት ተዓምራትን በቅዱስ መንፈስ የሚገልጥ ኣምላክ ኣለ ማለት ይሆናል።

Naga Tuma
Member+
Posts: 7781
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ግምታዊ የትንቢት መፈጸም በአራት ቃላት

Post by Naga Tuma » Yesterday, 12:59

የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቤተ መቅደስ፣ ቅዱስ መንፈስ ይታደስ እንጂ ኣይክሰም ማለት ማንን በደለ?

ቅዱስ መንፈስ ዬለም ከሚሉት በቀር።

Naga Tuma
Member+
Posts: 7781
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ግምታዊ የትንቢት መፈጸም በአራት ቃላት

Post by Naga Tuma » Yesterday, 13:29

የሰዉ ልጅ የመጀመርያዉ ጥበብ ፈጣሪን ማወቅ ነዉ። ፈጣሪን ማወቅ ቅዱስ መንፈስን ማክበር ነዉ።

ፈጣሪን የማያዉቅ ኣሕዛብ ነዉ።

Naga Tuma
Member+
Posts: 7781
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ግምታዊ የትንቢት መፈጸም በአራት ቃላት

Post by Naga Tuma » Yesterday, 14:48

ልጅ ኢሳያስ ገብረ እስራኤል፥

የዐለም ሰገድ ቅዱስ መንፈስ የምያዉቅህ ይሆን?

የማያዉቅህ ከሆነ በምን ተዓምር የኣንተን መልዕክተኛ ሰኔ ማርያም ቀን፣ 2017፣ ዓም የመጀመርያዉ መለኮታዊ ብይን ተቀባይ ኣደረገዉ? ሰዎች መለኮትን ፍሩ፥ ቁጥር 2

ከዐለም ሰገድ ቅዱስ መንፈስ ጋር ያለህ ጥል ኣለ?

ለመሆኑ የአኙዋ ጎሳ መስገድን ከመሠረቱ የምያዉቁ መሆናቸዉን ኣጥንተህ ታዉቃለህ?

Post Reply