እንደ ምታውቁት ቴዲ አፍሮ እስከ ዛሬ ድረስ አንድም የጉራጌኛ ዘፈን ዘፍኖ አያውቅም ነበር ።
ለምንድን ነው ኢቶሪካ ውስጥ ጉራጌኛ ዘፈን የጨመረው? መጨመር ብቻ ሳይሆን ጉሬጌ የተባለው ዜማ አሁን በዚህ ሰዓት ከ8 ሚሊዮን ግዜ በላይ እየተሰማ ከ18ቱ ዘፈኖቹ 2ኛ ሆኖ እየተደመጠ ያለ ዜማ ነው!
በዚህ ዜማ ውስጥ ቴዲ አፍሮ አባይ እየሞላ እንጎድላለን እኛ ብሉ ያዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛውን ግብር ቢከፍልም በወያኔን በአቢይም ተረስቶ የተተወው ምራብ አዲስ አበባ ነው ። የቴዲ ቅኔ አለምንም ጥርጥር የተቀኘው ስለጎደለስ ፣ ስለተቀነሰው ስለተረሳው መርካቶና ምራብ አዲሳባ ነው የተቀኘው ። ይህ ብቻ ሳይሆን ቴዲ አፍሮ ስለ መዘመን ያነሳው በዚህ ዜማ ውስጥ ብቻ ነው ።
ስምምነነ የተሰኘው ጉራጌኛ ዘፈን አይደለም በመርካቶ ፣ አይደለም ድፍን የጎርጊስ ቲፎዞ በሆነው ምራብ አዲሳባ በሰሜን አሜሪካ አገር ቶፕ 30 ዘፈኖች 27 ወይም 28ኛ ነው። ልብ በሉ አሜሪካን አገር ። ዳስ ጣል 13ኛ ነው ።
ስለዚህም ይመስለላል ዛሬ ቀን አዳነች አቤቤ የቅጠል ተራ መርካቶን ነዋሪ ሰብስባ የሚከተለውን ትላለች!
ግን የሚገርመው ይህን መሰረት መጣል የማደርገው ለምርጫ ወይም ለሽንገላ ወይም ለፕሮፓጋንዳ አይደለም ብላለች! ይህን አባባል ምን አመጣው?
ለማንኛውም ለቴድ መራር ትችች መልሱ ቢያንስ ይህን መሰል ነገር እንጂ ክራርና ማሲንቆውን መስበርና መስረቅ አይደለም!
ንግግሯ መጨረሻ ላይ በቀጥታ ለቴዲ ስትመልስ ስሙት!