Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 26 Mar 2026, 02:09

26/03/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - ንሕና ብኢየሱስ ክርስቶስ ጥራሕ ኢና እንምካሕ ዘሎና፡ ግዳማዊ ስርዓት፡ ንመንፈሳዊ ሕይወትና፡ ዝጠቕም የብሉን፡ ምእንቲ እቲ መዘና ዘይብሉ ፍልጠት ጐይታና ኢየሱስ ክርስቶስ ንዅሉ ነገር ከም ክሳራ ንቖጽሮ ኣሎና።
ፊሊ፡ 3፡ 1-11
1 በቀረውስ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ በጌታ ደስ ይበላችሁ። ስለ አንድ ነገር መልሼ ልጽፍላችሁ እኔን አይታክተኝም ለእናንተ ግን ደኅና ነው።
2 ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ከሐሰተኛም መገረዝ ተጠበቁ።
3 እኛ በመንፈስ እግዚአብሔርን የምናመልክ በክርስቶስ ኢየሱስም የምንመካ በሥጋም የማንታመን እኛ የተገረዝን ነንና።
4 እኔ ግን በሥጋ ደግሞ የምታመንበት አለኝ። ሌላ ሰው ማንም ቢሆን በሥጋ የሚታመንበት እንዳለው ቢመስለው፥ እኔ እበልጠዋለሁ።
5 በስምንተኛው ቀን የተገረዝሁ፥ ከእስራኤል ትውልድ፥ ከብንያም ወገን፥ ከዕብራውያን ዕብራዊ ነኝ፤ ስለ ሕግ ብትጠይቁ፥ ፈሪሳዊ ነበርሁ፤
6 ስለ ቅንዓት ብትጠይቁ፥ ቤተ ክርስቲያንን አሳዳጅ ነበርሁ፤ በሕግ ስለሚገኝ ጽድቅ ብትጠይቁ፥ ያለ ነቀፋ ነበርሁ።
7 ነገር ግን ለእኔ ረብ የነበረውን ሁሉ ስለ ክርስቶስ እንደ ጉዳት ቈጥሬዋለሁ።
8 - 9 አዎን፥ በእውነት ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤ ስለ እርሱ ሁሉን ተጐዳሁ፥ ክርስቶስንም አገኝ ዘንድ፥ በክርስቶስም በማመን ያለው ጽድቅ ማለት በእምነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ያለው ጽድቅ እንጂ ከሕግ ለእኔ ያለው ጽድቅ ሳይሆንልኝ፥ በእርሱ እገኝ ዘንድ ሁሉን እንደ ጕድፍ እቈጥራለሁ፤
10 - 11 እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ።

ቀስተ ጸሎት፡ - ንኣኡ እረክብን ምሳኡ ክኸውንን ንዅሉ ከም ጉሓፍ እቆጽሮ ኣሎኹ።
መዝ 123፡ 1 - ፍጻሜ
1በሰማይ የምትኖር ሆይ፥ ዓይኖቼን ወደ አንተ አነሣሁ።
2 እነሆ፥ የባሪያዎች ዓይኖች ወደ ጌታቸው እጅ እንደ ሆኑ፥ የባሪያይቱም ዓይን ወደ እመቤትዋ እጅ እንደ ሆነ፥ እንዲሁ እስኪምረን ድረስ ዓይናችን ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ነው።
3 ማረን፥ አቤቱ፥ ማረን፤ ንቀትን እጅግ ጠግበናልና፤
4 የባለጠጎች ስድብና የትዕቢተኞችን ንቀት ነፍሳችን እጅግ ጠገበች።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 27 Mar 2026, 02:39

27/03/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - እታ ናብ ሕያውነት ዘለዓለም እትወስድ ኣፍደገ ጸባብ እያ’ሞ ንርእስና ብምግታእን ብተጋድሎን ንውረሳ።
ማቴ 7፡ 13-15
13 በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤
14 ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።
15 የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።

ቀስተ ጸሎት፡ - ኦ እግዚኣብሔር ጎደናታትካ ኣፍልጠኒ።
መዝ 25፡4-ፍጻሜ
4 አቤቱ፥ መንገድህን አመልክተኝ፥ ፍለጋህንም አስተምረኝ።
5 አንተ የመድኃኒቴ አምላክ ነህና በእውነትህ ምራኝ፥ አስተምረኝም፤ ቀኑን ሁሉ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁ።
6 አቤቱ፥ ምሕረትህንና ቸርነትህን አስብ፥ ከጥንት ጀምሮ ናቸውና።
7 የልጅነቴን ኃጢአትና መተላለፍ አታስብብኝ፤ አቤቱ፥ ስለ ቸርነትህ ብዛት እንደ ምሕረትህ አስበኝ።
8 እግዚአብሔር ቸር ቅንም ነው፤ ስለዚህ ኃጢአተኞችን በመንገድ ይመራቸዋል።
9 ገሮችን በፍርድ ይመራል፥ ለገሮችም መንገድን ያስተምራቸዋል።
10 የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ነው። ቃል ኪዳኑንና ምስክሩን ለሚጠብቁ።
11 አቤቱ፥ ኃጢአቴ እጅግ ነውና ስለ ስምህ ይቅር በለኝ።
12 እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማን ነው? በሚመርጠው መንገድ ያስተምረዋል።
13 ነፍሱ በመልካም ታድራለች፥ ዘሩም ምድርን ይወርሳል።
14 እግዚአብሔር ለሚፈሩት ኃይላቸው ነው፥ ቃል ኪዳኑንም ያስታውቃቸዋል።
15 እርሱ እግሮቼን ከወጥመድ ያወጣቸዋልና ዓይኖቼ ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር ናቸው።
16 እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም።
17 የልቤ ችግር ብዙ ነው፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ።
18 ድካሜንና መከራዬን እይ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ።
19 ጠላቶቼ እንደ በዙ እይ፥ የግፍም ጥል ጠልተውኛል።
20 ነፍሴን ጠብቅና አድነኝ፤ አንተን ታምኛለሁና አልፈር።
21 አንተን ተስፋ አድርጌአለሁና የውሃትና ቅንነት ይጠብቁኝ።
22 አቤቱ፥ እስራኤልን ከመከራው ሁሉ አድነው።


Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 28 Mar 2026, 03:14

28/03/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - እግዚኣብሔር ብዝተፈላለየ መንገዲ ይዛረበና ኢዩ’ሞ ጽን ኢልና ንስምዓዮ።
ዕብ 4፡ 7-14
7 ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ በፊት እንደ ተባለ፥ ይህን ከሚያህል ዘመን በኋላ በዳዊት ሲናገር። ዛሬ ብሎ አንድ ቀን እንደ ገና ይቀጥራል።
8 ኢያሱ አሳርፎአቸው ኖሮ ቢሆንስ፥ ከዚያ በኋላ ስለ ሌላ ቀን ባልተናገረ ነበር።
9 እንግዲያስ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ቀርቶላቸዋል።
10 ወደ ዕረፍቱ የገባ፥ እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ፥ እርሱ ደግሞ ከሥራው አርፎአልና።
11 እንግዲህ እንደዚያ እንደ አለመታዘዝ ምሳሌ ማንም እንዳይወድቅ ወደዚያ ዕረፍት ለመግባት እንትጋ።
12 የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤
13 እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።
14 እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥ ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ።


ቀስተ ጸሎት፡ - ሎሚ ድማ ቃሉ እንተሰማዕኩም ልብኹም ኣይተትርሩ።
መዝ 3፡1-8
1 አቤቱ፥ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ! በኔ ላይ የሚቆሙት ብዙ ናቸው።
2 ብዙ ሰዎች ነፍሴን። አምላክሽ አያድንሽም አልዋት።
3 አንተ ግን አቤቱ፥ መጠጊያዬ ነህ፥ ክብሬንና ራሴንም ከፍ ከፍ የምታደርገው አንተ ነህ።
4 በቃሌ ወደ እግዚአብሔር እጮሃለሁ ከተቀደሰ ተራራውም ይሰማኛል።
5 እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፤ እግዚአብሔርም ደግፎኛልና ነቃሁ።
6 ከሚከብቡኝ ከአእላፍ ሕዝብ አልፈራም።
7 ተነሥ፥ አቤቱ፤ አምላኬ ሆይ፥ አድነኝ፤ አንተ የጠላቶቼን መንጋጋ መትተሃልና፥ የክፉዎችንም ጥርስ ሰብረሃልና።
8 ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥ በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 28 Mar 2026, 04:33

29/03/2026 - ሰንበት ዘኒቆዲሞስ

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - መዓልቲ ጐይታ ከም ሰራቒ ንነፍስወከፍና ክትመጸና ኢያ፡ ስለዚ ከኣ ብቕዱስ ሕይወትን ብፍርኃት እግዚኣብሔርን ክንነብር ኢዩ ዝግብኣና። ብዘይ ነውርን መንቅብን ምስ ክርስቶስ ሰላም ዘሎና ኮይንና ክንርከብ ንጋደል።
2ጴጥ 3፡ 3-15
3 በመጨረሻው ዘመን እንደ ራሳቸው ምኞት የሚመላለሱ ዘባቾች በመዘበት እንዲመጡ ይህን በፊት እወቁ፤
4 እነርሱም። የመምጣቱ የተስፋ ቃል ወዴት ነው? አባቶች ከሞቱባት ጊዜ፥ ከፍጥረት መጀመሪያ ይዞ ሁሉ እንዳለ ይኖራልና ይላሉ።
5 ሰማያት ከጥንት ጀምረው ምድርም በእግዚአብሔር ቃል ከውኃ ተጋጥማ በውኃ መካከል እንደ ነበሩ ወደው አያስተውሉምና፤
6 በዚህም ምክንያት ያን ጊዜ የነበረ ዓለም በውኃ ሰጥሞ ጠፋ፤
7 አሁን ያሉ ሰማያትና ምድር ግን እግዚአብሔርን የማያመልኩት ሰዎች እስከሚጠፉበት እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ተጠብቀው በዚያ ቃል ለእሳት ቀርተዋል።
8 እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፥ በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺህ ዓመት፥ ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን እንደ ሆነ ይህን አንድ ነገር አትርሱ።
9 ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።
10 የጌታው ቀን ግን እንደ ሌባ ሆኖ ይመጣል፤ በዚያም ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፥ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይቀልጣል፥ ምድርም በእርስዋም ላይ የተደረገው ሁሉ ይቃጠላል።
11 - 12 ይህ ሁሉ እንዲህ የሚቀልጥ ከሆነ፥ የእግዚአብሔርን ቀን መምጣት እየጠበቃችሁና እያስቸኰላችሁ፥ በቅዱስ ኑሮ እግዚአብሔርንም በመምሰል እንደ ምን ልትሆኑ ይገባችኋል? ስለዚያ ቀን ሰማያት ተቃጥለው ይቀልጣሉ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይፈታል፤
13 ነገር ግን ጽድቅ የሚኖርባትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እንደ ተስፋ ቃሉ እንጠብቃለን።
14 ስለዚህ፥ ወዳጆች ሆይ፥ ይህን እየጠበቃችሁ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ሆናችሁ በሰላም በእርሱ እንድትገኙ ትጉ፥
15 የጌታችንም ትዕግሥት መዳናችሁ እንደ ሆነ ቍጠሩ። እንዲህም የተወደደው ወንድማችን ጳውሎስ ደግሞ እንደ ተሰጠው ጥበብ መጠን ጻፈላችሁ፥ በመልእክቱም ሁሉ ደግሞ እንደ ነገረ ስለዚህ ነገር ተናገረ።

ቀስተ ጸሎት፡ - እምበኣር ንንቃሕ ገዛእ ርእስናውን ንግታእ ደኣ እምበር ከምቶም ካልኦት ደቀስቲ ኣይንኹን። (1 ተሰ 4፡6)
መዝ 50፡ 2-3
2 ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል።
3 አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይቃጠላል፥ በዙሪያውም ብዙ ዐውሎ አለ።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 30 Mar 2026, 02:17

30/03/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - ንሓድሕድና ንፋቐርን ብፍቕሪ ንንበርን፡ ፍቕሪ ማለት ከኣ ትእዛዛት ኣምላኽ እናፈጸምካ ምንባር ማለት እዩ። (2ይ ዮሓ 1፡6)
ሉቃ 13፡ 22-30
22 ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ ከተማዎችንና መንደሮችን እያስተማረ ያልፍ ነበር።
23 አንድ ሰውም። ጌታ ሆይ፥ የሚድኑ ጥቂቶች ናቸውን? አለው። እርሱም እንዲህ አላቸው።
24 በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ፤ እላችኋለሁና፥ ብዙዎች ሊገቡ ይፈልጋሉ አይችሉምም።
25 ባለቤቱ ተነሥቶ በሩን ከቈለፈ በኋላ፥ እናንተ በውጭ ቆማችሁ። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ ክፈትልን እያላችሁ በሩን ልታንኳኩ ትጀምራላችሁ እርሱም መልሶ። ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም ይላችኋል።
26 በዚያን ጊዜም። በፊትህ በላን ጠጣንም በአደባባያችንም አስተማርህ ልትሉ ትጀምራላችሁ፤
27 እርሱም። እላችኋለሁ፥ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም፤ ሁላችሁ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ይላችኋል።
28 አብርሃምንና ይስሐቅን ያዕቆብንም ነቢያትንም ሁሉ በእግዚአብሔር መንግሥት ባያችሁ ጊዜ፥ እናንተ ግን ወደ ውጭ ተጥላችሁ ስትቀሩ፥ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
29 ከምሥራቅና ከምዕራብም ከሰሜንና ከደቡብም ይመጣሉ፥ በእግዚአብሔርም መንግሥት በማዕድ ይቀመጣሉ።
30 እነሆም፥ ከኋለኞች ፊተኞች የሚሆኑ አሉ፥ ከፊተኞችም ኋለኞች የሚሆኑ አሉ።

ቀስተ ጸሎት፡ - “ኣፍቅርሞ፡ ድላይካ ግበር።” (ቅዱስ ኣጎስጢኖስ)
መዝ 118፡ 19-20
19 የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ፤ ወደ እነርሱ ገብቼ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።
20 ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት፤ ወደ እርስዋ ጻድቃን ይገባሉ።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 31 Mar 2026, 01:48

31/03/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - ውሉድ ኣምላኽ ስለዝኾንና ብመንፈስ ኣምላኽ ክንምራሕ’ሞ እቲ ናብ ሞት ዝመርሓና ፍቓድ/ትምኒት ስጋና ክንሰቕሎ/ክንቐትሎ ይጽውዓና።
ሮሜ 8፡12-17
12 እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕዳ አለብን፥ እንደ ሥጋ ፈቃድ ግን እንኖር ዘንድ ለሥጋ አይደለም።
13 እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞቱ ዘንድ አላችሁና፤ በመንፈስ ግን የሰውነትን ሥራ ብትገድሉ በሕይወት ትኖራላችሁ።
14 በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።
15 አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።
16 የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል።
17 ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።

ቀስተ ጸሎት፡ - እቶም ኵሉ ግዜ እናወደሱኻ ኣብ ቤትካ ዝነብሩ፣ ኣየ ክንደይ ተዓዊቶም። (መዝ 84፡4)
መዝ 84፡1-12
1የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ ማደሪያዎችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው!
2 ነፍሴ የእግዚአብሔርን አደባባዮች ትወድዳለች ትናፍቅማለች፤ ልቤም ሥጋዬም በሕያው አምላክ ደስ ተሰኘ።
3 ወፍ ለእርስዋ ቤትን አገኘች፥ ዋኖስም ጫጩቶችዋን የምታኖርበት ቤት አገኘች፤ የሠራዊት አምላክ ንጉሤም አምላኬም ሆይ፥ እርሱ መሠዊያህ ነው።
4 በቤትህ የሚኖሩ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው፤ ለዓለምና ለዘላለምም ያመሰግኑሃል።
5 አቤቱ፥ እርዳታው ከአንተ ዘንድ የሆነለት፥ በልቡም የላይኛውን መንገድ የሚያስብ ሰው ምስጉን ነው።
6 በልቅሶ ሸለቆ ውስጥ በወሰነው ስፍራ የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና።
7 ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ፤ የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል።
8 የሠራዊት አምላክ አቤቱ፥ ጸሎቴን ስማ፤ የያዕቆብ አምላክ ሆይ፥ አድምጥ።
9 አቤቱ፥ መታመናችንን እይልን፥ ወደ ቀባኸውም ፊት ተመልከት።
10 ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች፤ በኃጥኣን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ።
11 እግዚአብሔር አምላክ ምሕረትንና እውነትን ስለ ወደደ፥ ሞገስንና ክብርን ይሰጣል፤ እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ከመልካም ነገር አያሳጣቸውም።
12 የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ በአንተ የታመነ ሰው ምስጉን ነው።


Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 01 Apr 2026, 01:40

01/04/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - ኣብዚ ናይ ጾም ግዜ፣ ብንስሓ ክፉእ ግብርና እናተኣመንና፡ ብኑዛዜን ጣዕሳን ንልብና ክንፍትሽ፣ ስም እግዚኣብሔር ብኣና ክኸብር ብትሑት ልቢ ንቕረብ።
ግ.ሓ. 19፡8-20
8 ወደ ምኵራብም ገብቶ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት እየተነጋገረና እያስረዳቸው ሦስት ወር ያህል በግልጥ ይናገር ነበር።
9 አንዳንዶች ግን እልከኞች ሆነው በሕዝብ ፊት መንገዱን እየሰደቡ ባላመኑ ጊዜ፥ ከእነርሱ ርቆ ደቀ መዛሙርትን ለየ፥ ጢራኖስም በሚሉት በትምህርት ቤት ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር።
10 በእስያም የኖሩት ሁሉ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም የጌታን ቃል እስኪሰሙ ድረስ ሁለት ዓመት ያህል እንዲህ ሆነ።
11 እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር፤ ስለዚህም ከአካሉ ጨርቅ ወይም ልብስ ወደ ድውዮች ይወስዱ ነበር፥
12 ደዌያቸውም ይለቃቸው ነበር ክፉዎች መናፍስትም ይወጡ ነበር።
13 አጋንንትንም እያወጡ ይዞሩ ከነበሩት አይሁድ አንዳንዶች። ጳውሎስ በሚሰብከው በኢየሱስ እናምላችኋለን እያሉ ክፉዎች መናፍስት ባሉባቸው ላይ የጌታን የኢየሱስን ስም ይጠሩባቸው ዘንድ ሞከሩ።
14 የካህናትም አለቃ ለሆነ አስቄዋ ለሚሉት ለአንድ አይሁዳዊ ይህን ያደረጉ ሰባት ልጆች ነበሩት።
15 ክፉው መንፈስ ግን መልሶ። ኢየሱስንስ አውቀዋለሁ ጳውሎስንም አውቀዋለሁ፤ እናንተሳ እነማን ናችሁ? አላቸው።
16 ክፉው መንፈስም ያለበት ሰው ዘለለባቸው ቆስለውም ከዚያ ቤት ዕራቁታቸውን እስኪሸሹ ድረስ በረታባቸው አሸነፋቸውም።
17 ይህም በኤፌሶን በሚኖሩት ሁሉ በአይሁድና በግሪክ ሰዎች ዘንድ የታወቀ ሆነ፥ በሁላቸውም ላይ ፍርሃት ወደቀባቸው፥ የጌታም የኢየሱስ ስም ተከበረ፤
18 አምነውም ከነበሩት እጅግ ሰዎች ያደረጉትን እየተናዘዙና እየተናገሩ ይመጡ ነበር።
19 ከአስማተኞችም ብዙዎቹ መጽሐፋቸውን ሰብስበው በሰው ሁሉ ፊት አቃጠሉት፤ ዋጋውም ቢታሰብ አምሳ ሺህ ብር ሆኖ ተገኘ።
20 እንዲህም የጌታ ቃል በኃይል ያድግና ያሸንፍ ነበር።

ቀስተ ጸሎት፡ - ኦ ኣምላኽ መርምረኒ፡ ልበይከኣ ፍለጥ። ፈትነኒ፡ ሓሳበይ’ውን ፍለጥ። መንገዲ ዓመጻ እንተኣሊዩኒ ርኣ፡ በቲ ናይ ዘልዓለም መንገዲ ምርሓኒ።
መዝ 18፡1-14
1 አቤቱ ጕልበቴ ሆይ፥ እወድድሃለሁ።
2 እግዚአብሔር ዓለቴ፥ አምባዬ፥ መድኃኒቴ፥ አምላኬ፥ በእርሱም የምተማመንበት ረዳቴ፥ መታመኛዬና የደኅንነቴ ቀንድ መጠጊያዬም ነው።
3 ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርን እጠራለሁ፥ ከጠላቶቼም እድናለሁ።
4 የሞት ጣር ያዘኝ፥ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ፤
5 የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድም ደረሰብኝ።
6 በጨነቀኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፥ ወደ አምላኬም ጮኽሁ፤ ከመቅደሱም ቃሌን ሰማኝ፥ ጩኸቴም በፊቱ ወደ ጆሮው ገባ።
7 ምድርም ተንቀጠቀጠች ተናወጠችም፥ የተራሮችም መሠረቶች ተነቃነቁ፥ እግዚአብሔርም ተቈጥቶአልና ተንቀጠቀጡ።
8 ከቍጣው ጢስ ወጣ፥ ከፊቱም የሚበላ እሳት ነደደ፤ ፍምም ከእርሱ በራ።
9 ሰማዮችን ዝቅ ዝቅ አደረገ ወረደም፥ ጨለማ ከእግሩ በታች ነበረ።
10 በኪሩቤልም ላይ ተቀምጦ በረረ፥ በነፋስም ክንፍ በረረ።
11 መሰወሪያውን ጨለማ አደረገ፤ በዙሪያውም ድንኳኑ፤ በደመናት ውስጥ የጨለማ ውኃ ነበረ።
12 በፊቱ ካለው ብርሃን የተነሣ ደመናትና በረዶ የእሳት ፍምም አለፉ።
13 እግዚአብሔርም ከሰማያት አንጐደጐደ፥ ልዑልም ቃሉን ሰጠ።
14 ፍላጻውን ላከ በተናቸውም፤ መብረቆችን አበዛ አወካቸውም።
Last edited by Meleket on 06 Apr 2026, 03:31, edited 1 time in total.

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 02 Apr 2026, 01:29

02/04/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - ኣብዛ ምድሪ ኣጋይሽን ስደተኛታትን ምዃና ኵሉ ግዜ ክንዝክር፡ ነታ ሰማያዊት ሃገርና እናሓሰብና ብእምነት ጸኒዕና ብጥበብን ብምስትውዓልን ክንነብረሉ ዘሎና ግዜ ንጠቐመሉ።
ዕብ 11፡1-16
1 እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።
2 ለሽማግሌዎች የተመሰከረላቸው በዚህ ነውና።
3 ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተዘጋጁ፥ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን።
4 አቤል ከቃየል ይልቅ የሚበልጥን መሥዋዕት ለእግዚአብሔር በእምነት አቀረበ፥ በዚህም፥ እግዚአብሔር ስለ ስጦታው ሲመሰክር፥ እርሱ ጻድቅ እንደ ሆነ ተመሰከረለት፤ ሞቶም ሳለ በመሥዋዕቱ እስከ አሁን ይናገራል።
5 ሄኖክ ሞትን እንዳያይ በእምነት ተወሰደ፥ እግዚአብሔርም ስለ ወሰደው አልተገኘም። ሳይወሰድ እግዚአብሔርን ደስ እንዳሰኘ ተመስክሮለታልና፤
6 ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና።
7 ኖኅ ገና ስለማይታየው ነገር ተረድቶ እግዚአብሔርን እየፈራ ቤተ ስዎቹን ለማዳን መርከብን በእምነት አዘጋጀ፥ በዚህም ዓለምን ኰነነ፥ በእምነትም የሚገኘውን ጽድቅ ወራሽ ሆነ።
8 አብርሃም የተባለው ርስት አድርጎ ሊቀበለው ወዳለው ስፍራ ለመውጣት በእምነት ታዘዘ፥ ወዴትም እንደሚሄድ ሳያውቅ ወጣ።
9 ለእንግዶች እንደሚሆን በተስፋ ቃል በተሰጠው አገር በድንኳን ኖሮ፥ ያን የተስፋ ቃል አብረውት ከሚወርሱ ከይስሐቅና ከያዕቆብ ጋር፥ እንደ መጻተኛ በእምነት ተቀመጠ፤
10 መሠረት ያላትን፥ እግዚአብሔር የሠራትንና የፈጠራትን ከተማ ይጠብቅ ነበርና።
11 ተስፋ የሰጠው የታመነ እንደ ሆነ ስለ ቈጠረች፥ ሣራ ራስዋ ደግሞ ዕድሜዋ እንኳ ካለፈ በኋላ ዘርን ለመፅነስ ኃይልን በእምነት አገኘች።
12 ስለዚህ ደግሞ በብዛታቸው እንደ ሰማይ ኮከብ እንደማይቈጠርም በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ የነበሩት የሞተን ሰው እንኳ ከመሰለው ከአንዱ ተወለዱ።
13 እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ፥ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል አላገኙምና፤ ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አዩትና ተሳለሙት፥ በምድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንዲሆኑ ታመኑ።
14 እንዲህ የሚሉት ለእነርሱ የሚሆነውን አገር እንዲፈልጉ ያመለክታሉና።
15 ያን የወጡበትን አገር አስበው ቢሆኑ፥ ሊመለሱ ጊዜ በሆነላቸው ነበር፤
16 አሁን ግን የሚበልጠውን እርሱም ሰማያዊ አገር ይናፍቃሉ። ስለዚህ እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ በእነርሱ አያፍርም፥ ከተማን አዘጋጅቶላቸዋልና።

ቀስተ ጸሎት፡ - ንሕግኻ ክሳብ ዕለተ ሞተይ ክሕልዎ ኣንቂደ ኣለኹ። (መዝ 119፡112)
መዝ 103፡17-18
17 የእግዚአብሔር ምሕረት ግን ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚፈሩት ላይ፥ ጽድቁም በልጅ ልጆች ላይ ነው፤
18 ቃል ኪዳኑን በሚጠብቁ፥ ትእዛዙንም ያደርጉአት ዘንድ በሚያስቡ ላይ ነው።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 03 Apr 2026, 01:43

03/04/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - ክንጽሊ እንከለና ተኣምራት ንጸበ። ከምቲ ኢየሱስ ኣብ ደብረታቦር ክጽሊ ምስ ጀመረ ትርኢቱ ዝተለወጠ፡ ሕጂ ክንልወጥ፣ ክንሓዊ፣ ትእምርቲን ተኣምራትን ብእምነት ንጸበ፡ ሽዑ ንቃል እግዚኣብሔር ብትብዓት ክንሰብኮ ኢና።
ግ.ሓ. 4፡ 23-35
23 ተፈትተውም ወደ ወገኖቻቸው መጡና የካህናት አለቆችና ሽማግሌዎች ያሉአቸውን ሁሉ ነገሩአቸው።
24 እነርሱም በሰሙ ጊዜ በአንድ ልብ ሆነው ወደ እግዚአብሔር ድምፃቸውን ከፍ አደረጉ እንዲህም አሉ። ጌታ ሆይ፥ አንተ ሰማዩንና ምድሩን ባሕሩንም በእነርሱም የሚኖረውን ሁሉ የፈጠርህ፥
25 በመንፈስ ቅዱስም በብላቴናህ በአባታችን በዳዊት አፍ። አሕዛብ ለምን አጕረመረሙ? ሕዝቡስ ከንቱን ነገር ለምን አሰቡ?
26 የምድር ነገሥታት ተነሡ አለቆችም በጌታና በተቀባው ላይ አብረው ተከማቹ ብለህ የተናገርህ አምላክ ነህ።
27 - 28 በቀባኸው በቅዱሱ ብላቴናህ በኢየሱስ ላይ ሄሮድስና ጴንጤናዊው ጲላጦስ ከአሕዛብና ከእስራኤል ሕዝብ ጋር፥ እጅህና አሳብህ እንዲሆን አስቀድመው የወሰኑትን ሁሉ ሊፈጽሙ፥ በዚች ከተማ በእውነት ተሰበሰቡ።
29 - 30 አሁንም፥ ጌታ ሆይ፥ ወደ ዛቻቸው ተመልከት፤ ለመፈወስም እጅህን ስትዘረጋ በቅዱስ ብላቴናህም በኢየሱስ ስም ምልክትና ድንቅ ሲደረግ፥ ባሪያዎችህ በፍጹም ግልጥነት ቃልህን እንዲናገሩ ስጣቸው።
31 ከጸለዩም በኋላ ተሰብስበው የነበሩበት ስፍራ ተናወጠ፥ በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ የእግዚአብሔርንም ቃል በግልጥ ተናገሩ።
32 ያመኑትም ሕዝብ አንድ ልብ አንዲትም ነፍስ ነበሩአቸው፥ ገንዘባቸውም ሁሉ በአንድነት ነበረ እንጂ ካለው አንድ ነገር ስንኳ የራሱ እንደ ሆነ ማንም አልተናገረም።
33 ሐዋርያትም የጌታን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ በታላቅ ኃይል ይመሰክሩ ነበር፤ በሁሉም ላይ ታላቅ ጸጋ ነበረባቸው።
34 በመካከላቸው አንድ ስንኳ ችግረኛ አልነበረምና፤ መሬት ወይም ቤት ያላቸው ሁሉ እየሸጡ የተሸጠውን ዋጋ ያመጡ ነበርና፥
35 በሐዋርያትም እግር አጠገብ ያኖሩ ነበር፤ ማናቸውም እንደሚፈልግ መጠን ለእያንዳንዱ ያካፍሉት ነበር።

ቀስተ ጸሎት፡ - ንዑ ንእግዚኣብሔር ብሓጎስ ንዘምር፡ ንኸውሒ ምድሓንና ዕልል ንበለሉ።
መዝ 95፡ 1-6
1 ኑ፥በእግዚአብሔር ደስ ይበለን፤ ለአምላክ ለመድኃኒታችን እልል እንበል።
2 በምስጋና ወደ ፊቱ እንድረስ፥ በዝማሬም ለእርሱ እልል እንበል፤
3 እግዚአብሔር ታላቅ አምላክ ነውና፥ በአማልክትም ሁሉ ላይ ታላቅ ንጉሥ ነውና።
4 እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥላቸውም፤ የምድር ዳርቻዎችም በእጁ ውስጥ ናቸው፥ የተራሮች ከፍታዎች የእርሱ ናቸው።
5 ባሕር የእርሱ ናት እርሱም አደረጋት፥ የብስንም እጆቹ ሠሩአት።
6 ኑ፥ እንስገድ ለእርሱም እንገዛ፤ በእርሱ ባደረገን በእግዚአብሔር ፊት እንበርከክ፤


Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 04 Apr 2026, 01:43

04/04/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - እግዚኣብሔር ኩሉ ግዜ ነቶም ናብኡ ዝምህለሉ የናግፎም ይሕልዎምን፡ ናብኡ ዝጥምቱን ዝዕቆቡን ከኣ ኣይሓፍሩን። ስለዚ ብዘጋጥመና ከቢድ ጸገማት ክንፈርህን ክንሽበርን የብልናን።
2ይ ዜና 20፡1-15
1፤ እንዲህም ሆነ፤ ከዚህ በኋላ የሞዓብና የአሞን ልጆች ከእነርሱም ጋር ምዑናውያን ኢዮሣፍጥን ሊወጉ መጡ።
2 ፤ ወሬኞችም መጥተው። ከባሕሩ ማዶ ከሶሪያ ታላቅ ሠራዊት መጥቶብሃል፤ እነሆም፥ ዓይንጋዲ በተባለች በሐሴሶን ታማር ናቸው ብለው ለኢዮሣፍጥ ነገሩት።
3 ፤ ኢዮሣፍጥም ፈራ፥ እግዚአብሔርንም ሊፈልግ ፊቱን አቀና፤ በይሁዳም ሁሉ ጾም አወጀ።
4 ፤ ይሁዳም እግዚአብሔርን ይፈልግ ዘንድ ተከማቸ፤ ከይሁዳ ከተሞችም ሁሉ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ መጡ።
5 ፤ ኢዮሣፍጥም በይሁዳና በኢየሩሳሌም ጉባኤ መካከል በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ በአዲሱ አደባባይ ፊት ቆመ፤
6 ፤ እንዲህም አለ። አቤቱ የአባቶቻችን አምላክ ሆይ፥ በሰማይ ያለህ አምላክ አንተ አይደለህምን? የአሕዛብንስ መንግሥታት ሁሉ የምትገዛ አንተ አይደለህምን? ኃይልና ችሎታ በእጅህ ነው፥ ሊቋቋምህም የሚችል የለም።
7 ፤ አምላካችን ሆይ፥ በዚህ ምድር የነበሩትን አሕዛብ ከሕዝብህ ከእስራኤል ፊት ያሳደድህ፥ ለወዳጅህም ለአብርሃም ዘር ለዘላለም የሰጠሃት አንተ አይደለህምን?
8 ፤ እነርሱም የተቀመጡባት፥ ለስምህም መቅደስን ሠርተውባት።
9 ፤ ክፉ ነገር፥ የፍርድ ሰይፍ ወይም ቸነፈር ወይም ራብ፥ ቢመጣብን ስምህ ባለበት በዚህ ቤት ፊትና በፊትህ ቆመን በመከራችን ወደ አንተ እንጮኻለን፥ አንተም ሰምተህ ታድነናለህ አሉ።
10 ፤ አሁንም፥ እነሆ፥ እስራኤል ከግብጽ ምድር በወጡ ጊዜ ያልፉባቸው ዘንድ ያልፈቀድህላቸው፥ ነገር ግን ፈቀቅ ብለው ያላጠፉአቸው፥ የአሞንና የሞዓብ ልጆች የሴይርም ተራራ ሰዎች፥
11 ፤ እነሆ፥ ለወሮታችን ክፋት ይመልሱልናል፤ ከሰጠኸንም ርስት ያወጡን ዘንድ መጥተዋል።
12 ፤ አምላካችን ሆይ፥ አንተ አትፈርድባቸውምን? ይህን የመጣብንን ታላቅ ወገን እንቃወም ዘንድ አንችልም፤ የምናደርገውንም አናውቅም፤ ነገር ግን ዓይኖቻችን ወደ አንተ ናቸው።
13 ፤ የይሁዳም ሰዎች ሁሉ ከሕፃናቶቻቸውና ከሚስቶቻቸው ከልጆቻቸውም ጋር በእግዚአብሔር ፊት ቆመው ነበር።
14 ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ ከአሳፍ ወገን በነበረው በሌዋዊው በማታንያ ልጅ በይዒኤል ልጅ በበናያስ ልጅ በዘካሪያስ ልጅ በየሕዚኤል ላይ በጉባኤው መካከል መጣ፤
15 ፤ እንዲህም አለ። ይሁዳ ሁሉ፥ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ፥ አንተም ንጉሡ ኢዮሣፍጥ፥ ስሙ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላችኋል። ሰልፉ የእግዚአብሔር ነው እንጂ የእናንተ አይደለምና ከዚህ ታላቅ ወገን የተነሣ አትፍሩ፥ አትደንግጡም።

ቀስተ ጸሎት፡ - እግዚኣብሔር ሠናይ ኢዩ ምሕረቱ ከኣ ዘልዓለማዊ እዩ’ሞ ኣመስግንዎ።
መዝ 107፡1-3
1 ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤
2 እግዚአብሔር ያዳናቸው፥ ከጠላቶች እጅ ያዳናቸው ይናገሩ።
3 ከምሥራቅና ከምዕራብ፥ ከሰሜንና ከባሕር፥ ከየአገሩ ሰበሰባቸው።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 04 Apr 2026, 02:46

05/04/2026 - ሰንበት ዘሆሳዕና

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - እግዚኣብሔር ኣምላኽ ምእንቲ ኽሰምዕ እዝነይ ከፈተለይ፡ ኣነውን ኣይአቤኹን፡ ኣየድሓርሓርኹን። ዝባነይ ንገረፍቲ ምዕጕርተይ ከኣ ንነጸይቲ ጸጕሪ ሃብኩ። ክጸርፉንን ጡፍ ክብሉለይን ከለዉን ገጸይ ኣይከወልኩን።

ጡፍ ክበሃለልካ/ኪ ከሎ እንታይ ግብረ መልሲ ምሃብካ/ኪ፧ ከምቲ ክርስቶስ ገጹ ዘይከወሎ’ዶ፧ ዋላስ . . . ፧

ኢሳይያስ 50፡ 4-7
4 ፤ የደከመውን በቃል እንዴት እንደምደግፍ አውቅ ዘንድ ጌታ እግዚአብሔር የተማሩትን ምላስ ሰጥቶኛል ማለዳ ማለዳ ያነቃኛል፥ እንደ ተማሪዎችም ትሰማ ዘንድ ጆሮዬን ያነቃቃል።
5 ፤ ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬን ከፍቶአል፥ እኔም ዓመፀኛ አልነበርሁም ወደ ኋላዬም አልተመለስሁም።
6 ፤ ጀርባዬን ለገራፊዎች ጕንጬንም ለጠጕር ነጪዎች ሰጠሁ፥ ፊቴንም ከውርደትና ከትፋት አልመለስሁም።
7 ፤ ጌታ እግዚአብሔር ይረዳኛልና ስለዚህ አልታወክሁም፤ ስለዚህም ፊቴን እንደ ባልጩት ድንጋይ አድርጌዋለሁ፥ እንዳላፍርም አውቃለሁ።

ቀስተ ጸሎት፡ - እምነተይ ከዓቢ ከም ተምሃራይ ምእንቲ ንቓልካ ክሰምዕ ኣእዛነይን ልበይን ክፈተለይ።
መዝ 21፡ 1-ፍጻሜ
1 አቤቱ፥ በኃይልህ ንጉሥ ደስ ይለዋል፤ በማዳንህ እጅግ ሐሤትን ያደርጋል።
2 የልቡን ፈቃድ ሰጠኽው፥ የከንፈሩንም ልመና አልከለከልኸውም።
3 በበጎ በረከት ደርሰህለታልና፤ ከክቡር ዕንቍ የሆነ ዘውድን በራሱ ላይ አኖርህ።
4 ሕይወትን ለመነህ ሰጠኸውም፥ ለረጅም ዘመን ለዘላለሙ።
5 በማዳንህ ክብሩ ታላቅ ነው፤ ክብርንና ምስጋናን ጨመርህለት።
6 የዘላለም በረከትን ሰጥተኸዋልና። በፊትህም ደስታ ደስ ታሰኘዋለህ።
7 ንጉሥ በእግዚአብሔር ተማምኖአልና፥ በልዑልም ምሕረት አይናወጥም።
8 እጅህ ጠላቶችህን ሁሉ ታግኛቸው፥ ቀኝህም የሚጠሉህን ሁሉ ታግኛቸው።
9 በተቈጣህም ጊዜ እንደ እሳት እቶን አድርጋቸው፤ እግዚአብሔር በቍጣው ያጠፋቸዋል፥ እሳትም ትበላቸዋለች።
10 ፍሬአቸውን ከምድር ዘራቸውንም ከሰው ልጆች ታጠፋለህ።
11 ክፋትን በአንተ ላይ ዘርግተዋልና፥ የማይቻላቸውንም ምክር አሰቡ።
12 ወደ ኋላቸው ትመልሳቸዋለህ፤ ፍላጻን በፊታቸው ላይ ታዘጋጃለህ።
13 አቤቱ፥ በኃይልህ ከፍ ከፍ በል፤ ጽናትህንም እናመሰግናለን እንዘምርማለን።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 06 Apr 2026, 03:30

06/04/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - ንሓዉ ዚጸልእ ዘበለ ዅሉ ቐታሊ ነፍሲ እዩ። ቀታል ነፍሲ ዝኾነ ዅሉ ድማ ናይ ዘለዓለም ሕይወት ከም ዘይብሉ ትፈልጡ ኢኹም።

ንኣሕዋትካ ጭራስ ጸሊእካዮም ትፈልጠሉ መዓልታት ኣሎካ’ዶ፧ በዚ ሓሳብ ኣብ መንበረ ኑዛዜ ቅረብ/ቢ!!
1ዮሓ 3፡11-18
11 ከመጀመሪያ የሰማችኋት መልእክት። እርስ በርሳችን እንዋደድ የምትል ይህች ናትና፤
12 ከክፉው እንደ ነበረ ወንድሙንም እንደ ገደለ እንደ ቃየል አይደለም፤ ስለ ምንስ ገደለው? የገዛ ሥራው ክፉ፥ የወንድሙም ሥራ ጽድቅ ስለ ነበረ ነው።
13 ወንድሞች ሆይ፥ ዓለም ቢጠላችሁ አትደነቁ።
14 እኛ ወንድሞችን የምንወድ ስለ ሆንን ከሞት ወደ ሕይወት እንደ ተሻገርን እናውቃለን፤ ወንድሙን የማይወድ በሞት ይኖራል።
15 ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው፥ ነፍሰ ገዳይም የሆነ ሁሉ የዘላለም ሕይወት በእርሱ እንዳይኖር ታውቃላችሁ።
16 እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል።
17 ነገር ግን የዚህ ዓለም ገንዘብ ያለው፥ ወንድሙም የሚያስፈልገው ሲያጣ አይቶ ያልራራለት ማንም ቢሆን፥ የእግዚአብሔር ፍቅር በእርሱ እንዴት ይኖራል?
18 ልጆቼ ሆይ፥ በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት አንዋደድ።

ቀስተ ጸሎት፡ - ከምቲ ዘፍቀርካኒ ከፍቅር ጸጋኻ ኣብዝሓለይ!
መዝ 38፡ 1-ፍጻሜ
1 አቤቱ፥ በቍጣህ አትቅሠፈኝ፥ በመዓትህም አትገሥጸኝ።
2 ፍላጾችህ ወግተውኛልና፥ እጅህንም አክብደህብኛልና።
3 ከቍጣህ የተነሣ ለሥጋዬ ጤና የለውም፤ ከኃጢአቴም የተነሣ ለአጥንቶቼ ሰላም የላቸውም።
4 ኃጢአቴ በራሴ ላይ ከፍ ከፍ ብሎአልና፥ እንደ ከባድ ሸክምም በላዬ ከብዶአልና።
5 ከስንፍናዬ የተነሣ ቍስሌ ሸተተ በሰበሰም፤
6 እጅግ ጐሰቈልሁ ተዋረድሁም፥ ሁልጊዜም በትካዜ እመላለሳለሁ።
7 ነፍሴ ስድብን ተሞልታለችና፥ ለሥጋዬም ጤና የላትምና።
8 ታመምሁ፤ እጅግም ተቸገርሁ፥ ከልቤ ውዝዋዜም የተነሣ ጮኽሁ።
9 አቤቱ፥ ፈቃዴ ሁሉ በፊትህ ነው፥ ጭንቀቴም ከአንተ አይሰወርም።
10 ልቤ ደነገጠብኝ፥ ኃይሌም ተወችኝ፥ የዓይኖቼም ብርሃን ፈዘዘ።
11 ወዳጆቼም ባልንጀሮቼም ከቍስሌ ገለል ብለው ቆሙ፥ ዘመዶቼም ርቀው ቆሙ።
12 ነፍሴንም የሚሹአት በረቱብኝ፥ መከራዬንም የሚፈልጉ ከንቱን ተናገሩ፥ ሁልጊዜም በሽንገላ ይመክራሉ።
13 እኔ ግን እንደማይሰማ ደንቆሮ አፉንም እንደማይከፍት ዲዳ ሆንሁ።
14 እንደማይሰማ ሰው በአፉም ተግሣጽ እንደሌለው ሰው ሆንሁ።
15 አቤቱ፥ በአንተ ታምኛለሁና፤ አቤቱ አምላኬ፥ አንተ ትሰማኛለህ።
16 ጠላቶቼ በእኔ ላይ ደስ እንዳይላቸው ብያለሁና፥ እግሮቼም ቢሰናከሉ ራሳቸውን በእኔ ላይ ከፍ ከፍ ያደርጋሉ።
17 እኔስ ወደ ማንከስ ቀርቤአለሁና፥ ቍስሌም ሁልጊዜም በፊቴ ነውና።
18 በደሌን እናገራለሁና፥ ስለ ኃጢአቴም እተክዛለሁ።
19 ጠላቶቼ ሕያዋን ናቸው ይበረቱብኝማል፥ በጠማማነትም የሚጠሉኝ በዙ።
20 ጽድቅን ስለ ተከተልሁ፥ በበጎ ፋንታ ክፉን የሚመልሱልኝ ይጠሉኛል።
21 አቤቱ፥ አንተ አትጣለኝ፤ አምላኬ፥ ከኔ አትራቅ።
22 አቤቱ መድኃኒቴ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 06 Apr 2026, 09:15

ዘሰሙነ ሕማማት - ሰኑይ

ኢሳይያስ ፶፡ ፭-፱
5 ፤ ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬን ከፍቶአል፥ እኔም ዓመፀኛ አልነበርሁም ወደ ኋላዬም አልተመለስሁም።
6 ፤ ጀርባዬን ለገራፊዎች ጕንጬንም ለጠጕር ነጪዎች ሰጠሁ፥ ፊቴንም ከውርደትና ከትፋት አልመለስሁም።
7 ፤ ጌታ እግዚአብሔር ይረዳኛልና ስለዚህ አልታወክሁም፤ ስለዚህም ፊቴን እንደ ባልጩት ድንጋይ አድርጌዋለሁ፥ እንዳላፍርም አውቃለሁ።
8 ፤ የሚያጸድቀኝ ቅርብ ነው፤ ከእኔስ ጋር የሚከራከር ማን ነው? በአንድነት እንቁም፤ የሚከራከረኝ ማን ነው? ወደ እኔ ይቅረብ።
9 ፤ እነሆ፥ ጌታ እግዚአብሔር ይረዳኛል፤ ማን ይፈርድብኛል? እነሆ፥ ሁሉ እንደ ልብስ ያረጃሉ ብልም ይበላቸዋል።

ምስባክ(መዝ ፹፪)
እስመ ተማከሩ ኅቡረ ወዐረዩ፡
ላዕሌከ ተሰካተዩ ወተካየዱ፡
ተዓይኒሆሙ ለኤዶምያስ ወለእስማኤላውያን።

ማቴ ፳፮፡ ፲፯ -፲፱
17 በቂጣው በዓል በመጀመሪያ ቀን ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ ቀርበው። ፋሲካን ትበላ ዘንድ ወዴት ልናሰናዳልህ ትወዳለህ አሉት።
18 እርሱም። ወደ ከተማ ከእገሌ ዘንድ ሄዳችሁ። መምህር። ጊዜዬ ቀርቦአል፤ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ከአንተ ዘንድ ፋሲካን አደርጋለሁ ይላል በሉት አለ።
19 ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ ፋሲካንም አሰናዱ።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 07 Apr 2026, 01:37

07/04/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - እቲ እግዚኣብሔር ነዞም ሕዝቢ እዚኦም ብነድሩን ብቝጥዓኡን ኣሰሚዑሎም ዘሎ መዓት ዓቢይ እዩ እሞ፡ ምናልባሽ ናብ እግዚኣብሔር ይምህለሉ፡ ነፍስ ወከፎም ከኣ ኻብ እኩይ መንገዶም ይምለሱ ይኾኑ ድማ በልኵዎ።

ካብቲ ካብ ገጽ እግዚኣብሔር ዘርሕቐካ መንገዲ ተመለስ! ሕጂ ምስ ኣምላኽኻ ኣዋግዕ!
1 ጴጥ 1፡1-9
1 የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ጴጥሮስ፥
2 እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ እንዳወቃቸው በመንፈስም እንደሚቀደሱ፥ ይታዘዙና በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ይረጩ ዘንድ ለተመረጡት በጳንጦስና በገላትያ በቀጰዶቅያም በእስያም በቢታንያም ለተበተኑ መጻተኞች፤ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።
3 -5 ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ ይህም ርስት በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል።
6 -7 በዚህም እጅግ ደስ ይላችኋል፥ ነገር ግን በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋው ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር የተፈተነ እምነታችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ፥ ለምስጋናና ለክብር ለውዳሴም ይገኝ ዘንድ አሁን ለጥቂት ጊዜ ቢያስፈልግ በልዩ ልዩ ፈተና አዝናችኋል።
8 - 9 እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ፥ የእምነታችሁን ፍፃሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ፥ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሤት ደስ ይላችኋል።

ቀስተ ጸሎት፡ - ኦ እግዚኣብሔር ንድምጺ ምህለላይ ስምዓዮ! ጓሂ ልበይውን ኣርሕቆ።
ኤር 36፡4-10
4 ኤርምያስም የኔርያን ልጀ ባሮክን ጠራ፥ ባሮክም እግዚአብሔር ለእርሱ የተናገረውን ቃል ሁሉ ከኤርምያስ አፍ በመጽሐፉ ክርታስ ጻፈ።
5 ኤርምያስም ባሮክን እንዲህ ሲል አዘዘው። እኔ ተግዤአለሁ፤ ወደ እግዚአብሔር ቤት እገባ ዘንድ አልችልም።
6 አንተ ግን ሂድ፥ ከአፌም የጻፍኸውን የእግዚአብሔርን ቃል በጾም ቀን በእግዚአብሔር ቤት በሕዝቡ ጆር በክርታሱ አንብብ፤ ደግሞም ከከተሞቻቸው በሚወጡ በይሁዳ ሰዎች ሁሉ ጆሮ አንብበው።
7 እግዚአብሔር በዚህ ሕዝብ ላይ የተናገረው ቍጣውና መዓቱ ታላቅ ነውና ምናልባት ጸሎታቸው በእግዚአብሔር ፊት ትወድቅ ይሆናል፥ ሁሉም ከክፉ መንገዱ ይመለስ ይሆናል።
8 የኔርያም ልጅ ባሮክ ነቢዩ ኤርምያስ ያዘዘውን ሁሉ አደረገ፥ በእግዚአብሔርም ቤት የእግዚአብሔርን ቃል በመጽሐፉ አነበበ።
9 እንዲህም ሆነ፤ በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም በአምስተኛው ዓመት በዘጠነኛው ወር በኢየሩሳሌም የተቀመጡ ሕዝብ ሁሉ ከይሁዳም ከተሞች ወደ ኢየሩሳሌም የመጡ ሕዝብ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ለመጾም አዋጅ ነገሩ።
10 ባሮክም የኤርምያስን ቃል በእግዚአብሄር ቤት በላይኛው አደባባይ በእግዚአብሔር ቤት በአዲሱ በር መግቢያ ባለው በጸሐፊው በሳፋን ልጅ በገማርያ ጓዳ በሕዝቡ ሁሉ ጆሮ በመጽሐፉ አነበበ።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 07 Apr 2026, 02:58

ዘሰሙነ ሕማማት - ሠሉስ

ኦሪት ዘፍጥረት ፳፪፡ ፮ - ፲
6 ፤ አብርሃምም የመሥዋዕቱን እንጨት አንሥቶ ለልጁ ለይስሐቅ አሸከመው፤ እርሱም እሳቱንና ቢላዋውን በእጁ ያዘ፥ ሁለቱም አብረው ሄዱ።
7 ፤ ይስሐቅም አባቱን አብርሃምን ተናገረው። አባቴ ሆይ አለ። እርሱም። እነሆኝ፥ ልጄ አለው። እሳቱና እንጨቱ ይኸው አለ፤ የመሥዋዕቱ በግ ግን ወዴት ነው? አለ።
8 ፤ አብርሃምም። ልጄ ሆይ፥ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው፤ ሁለቱም አብረው ሄዱ።
9 ፤ እግዚአብሔር ወዳለውም ቦታ ደረሱ፤ አብርሃምም በዚያ መሠዊያውን ሠራ፥ እንጨትንም ረበረበ፤ ልጁን ይስሐቅንም አስሮ በመሠዊያው በእንጨቱ ላይ አጋደመው።
10 ፤ አብርሃምም እጁን ዘረጋ፥ ልጁንም ያርድ ዘንድ ቢላዋ አነሣ።

ምስባክ(መዝ ፺፫)
ወይንዕዋ ለነፍሰ ጻድቅ፡
ወይኰንን ደመ ንጹሐ፡
ወኮነኒ እግዚኣብሔር ጸወንየ።

ማርቆስ ፲፬፡፩-፲፪
1 ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካና የቂጣ በዓል ነበረ። የካህናት አለቆችም ጻፎችም እንዴት አድርገው በተንኰል እንደሚይዙትና እንደሚገድሉት ይፈልጉ ነበር።
2 የሕዝብ ሁከት እንዳይሆን በበዓል አይሁን ይሉ ነበርና።
3 እርሱም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት በነበረ ጊዜ፥ በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የከበረ ጥሩ ናርዶስ ሽቱ የመላበት የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ ይዛ መጣች፤ ቢልቃጡንም ሰብራ በራሱ ላይ አፈሰሰችው።
4 አንዳንዶችም። ይህ የሽቱ ጥፋት ለምንድር ነው?
5 ይህ ሽቱ ከሦስት መቶ ዲናር በሚበልጥ ዋጋ ተሽጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበርና ብለው በራሳቸው ይቈጡ ነበር፤ እርስዋንም ነቀፉአት።
6 ኢየሱስ ግን እንዲህ አለ። ተዉአት፤ ስለ ምን ታደክሙአታላችሁ? መልካም ሥራ ሠርታልኛለች።
7 ድሆች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ በማናቸውም በወደዳችሁት ጊዜ መልካም ልታደርጉላቸው ትችላላችሁ፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም።
8 የተቻላትን አደረገች፤ አስቀድማ ለመቃብሬ ሥጋዬን ቀባችው።
9 እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለሙ ሁሉ በሚሰበክበት በማናቸውም ስፍራ፥ እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ ሊሆን ይነገራል።
10 ከአሥራ ሁለቱም አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ ሊሰጠው ወደ ካህናት አለቆች ሄደ።
11 ሲሰሙም ደስ አላቸው ብርም ይሰጡት ዘንድ ተስፋ ሰጡት። በሚመች ጊዜም እንዴት አድርጎ አሳልፎ እንዲሰጠው ይፈልግ ነበር።
12 ፋሲካን በሚያርዱበት በቂጣ በዓል መጀመሪያ ቀን ደቀ መዛሙርቱ። ፋሲካን ትበላ ዘንድ ወዴት ሄደን ልናሰናዳ ትወዳለህ? አሉት።

ኢሳይያስ ፶፫፡ ፩-፭
1 ፤የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?
2 ፤ በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
3 ፤ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።
4 ፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
5 ፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 08 Apr 2026, 02:01

08/04/2026

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - “መስዋዕትን መባእን ዝሓርር መስዋዕትን ምእንቲ ሓጢኣት ዝቐርብ መባኣን ኣይደሌኻን፡ ብኣኡዉን ባህ ኣይበለካን” ይብል ቃል ኣምላኽ።

ኣብ ሕይወትካ/ኪ ኣብ ክንዲ ሓጢኣትካ/ኪ መባእ፡ መስዋእቲ ተቕርበሎ እዋናት ኣሎ’ዶ፤ (ኣብ ክንዲ እዚ ምስ ሓውኻ/ኺ ተዓረቕ/ቒ ምሕረት ግበር/ሪ)
ዕብ 10፡ 4-10
4 የኮርማዎችና የፍየሎች ደም ኃጢአትን እንዲያስወግድ የማይቻል ነውና።
5 ስለዚህ ወደ ዓለም ሲገባ። መሥዋዕትንና መባን አልወደድህም ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ፤
6 በሙሉ በሚቃጠል መሥዋዕትና ሰለ ኃጢአት በሚሰዋ መሥዋዕት ደስ አላለህም።
7 በዚያን ጊዜ። እነሆ፥ በመጽሐፍ ጥቅልል ስለ እኔ እንደ ተጻፈ፥ አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ አልሁ
8 ይላል። በዚህ ላይ። መሥዋዕትንና መባን በሙሉ የሚቃጠል መሥዋዕትንም ስለ ኃጢአትም የሚሰዋ መሥዋዕትን አልወደድህም በእርሱም ደስ አላለህም ብሎ፥ እነዚህም እንደ ሕግ የሚቀርቡት ናቸው፥
9 ቀጥሎ። እነሆ፥ አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ ብሎአል። ሁለተኛውንም ሊያቆም የፊተኛውን ይሽራል።
10 በዚህም ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ አንድ ጊዜ ፈጽሞ በማቅረብ ተቀድሰናል።

ቀስተ ጸሎት፡ - ኦ ኣምላኸይ፡ ፍቃድኻ ክፍጽም መጺእ ኣሎኹ።
ራእይ 22፡ 1-ፍጻሜ
1 በአደባባይዋም መካከል ከእግዚአብሔርና ከበጉ ዙፋን የሚወጣውን እንደ ብርሌ የሚያንጸባርቀውን የሕይወትን ውኃ ወንዝ አሳየኝ።
2 በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት ዛፍ ነበረ፥ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ።
3 ከእንግዲህም ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም። የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል፥ ባሪያዎቹም ያመልኩታል፥ ፊቱንም ያያሉ፥
4 ስሙም በግምባሮቻቸው ይሆናል።
5 ከእንግዲህም ወዲህ ሌሊት አይሆንም፥ ጌታ አምላክም በእነርሱ ላይ ያበራላቸዋልና የመብራት ብርሃንና የፀሐይ ብርሃን አያስፈልጋቸውም፤ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ይነግሣሉ።
6 እርሱም። እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛዎች ናቸው፥ የነቢያትም መናፍስት ጌታ አምላክ በቶሎ ሊሆን የሚገባውን ነገር ለባሪያዎቹ እንዲያሳይ መልአኩን ሰደደ።
7 እነሆም፥ በቶሎ እመጣለሁ። የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ቃል የሚጠብቅ ብፁዕ ነው አለኝ።
8 ይህንም ያየሁትና የሰማሁት እኔ ዮሐንስ ነኝ። በሰማሁትና ባየሁትም ጊዜ ይህን ባሳየኝ በመልአኩ እግር ፊት እሰግድ ዘንድ ተደፋሁ።
9 እርሱም። እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር ከወንድሞችህም ከነቢያት ጋር የዚህንም መጽሐፍ ቃል ከሚጠብቁ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ አለኝ።
10 ለእኔም። ዘመኑ ቀርቦአልና የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ቃል በማኅተም አትዝጋው።
11 ዓመፀኛው ወደ ፊት ያምፅ፥ ርኵሱም ወደ ፊት ይርከስ፥ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ፥ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ አለ።
12 እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።
13 አልፋና ዖሜጋ፥ ፊተኛውና ኋለኛው፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ።
14 ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም ወደ ከተማይቱም እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው።
15 ውሻዎችና አስማተኞች ሴሰኛዎችም ነፍሰ ገዳዮችም ጣዖትንም የሚያመልኩት ውሸትንም የሚወዱና የሚያደርጉ ሁሉ በውጭ አሉ።
16 እኔ ኢየሱስ በአብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ይህን እንዲመሰክርላችሁ መልአኬን ላክሁ። እኔ የዳዊት ሥርና ዘር ነኝ፥ የሚያበራም የንጋት ኮከብ ነኝ።
17 መንፈሱና ሙሽራይቱም። ና ይላሉ። የሚሰማም። ና ይበል። የተጠማም ይምጣ፥ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው ይውሰድ።
18 በዚህ መጽሐፍ የተጻፈውን የትንቢት ቃል ለሚሰማ ሁሉ እኔ እመሰክራለሁ፤ ማንም በዚህ ላይ አንዳች ቢጨምር እግዚአብሔር በዚህ መጽሐፍ የተጻፉትን መቅሠፍቶች ይጨምርበታል፤
19 ማንምም በዚህ በትንቢት መጽሐፍ ከተጻፉት ቃሎች አንዳች ቢያጎድል፥ በዚህ መጽሐፍ ከተጻፉት ከሕይወት ዛፍና ከቅድስቲቱ ከተማ እግዚአብሔር ዕድሉን ያጎድልበታል።
20 ይህን የሚመሰክር። አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።
21 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።


Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 09 Apr 2026, 01:54

09/04/2026 - ጸሎተ ኃሙስ

መስተንተኒ ሓሳብ፡ - ኣታ ኣቦ ስድራ ዝኾንካ እስኪ ንምልክት ትሕትናኻ ንበዓልቲ ኪዳንካ ኣእጋራ ሕጸብ! ከምቲ ክርስቶስ ኣእጋር ሓዋርያት ዝሓጸቦ።
ዘጸ 12፡1-4
1 እግዚአብሔርም በግብፅ አገር ሙሴንና አሮንን እንዲህ ብሎ ተናገራቸው።
2 ፤ ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችሁ፤ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችሁ።
3 ፤ ለእስራኤል ልጆች ሁሉ ተናገሩ፥ በሉአቸውም። በዚህ ወር በአሥረኛው ቀን ሰው ሁሉ ለአባቱ ቤት አንድ ጠቦት፥ ለአንድ ቤትም አንድ ጠቦት ይውሰድ።
4 ፤ የቤቱ ሰዎች ቍጥርም ለጠቦቱ የማይበቃ ቢሆን እርሱና ለቤቱ የቀረበው ጎረቤቱ እንደ ነፍሶቻቸው ቍጥር አንድ ጠቦት ይውሰድ፤ እያንዳንዱም እንደሚበላው መጠን ከጠቦቱ ይካፈሉ።

ቀስተ ጸሎት፡ - ኦ ጐይታይ ንስጋኻን ደምካን ብምስትውዓል ንምቕባል ኣብቅዓኒ።
1ቆሮ 11፡23-34
23 ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠሁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለሁና፤
24 ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም። እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
25 እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ። ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
26 ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና።
27 ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት።
28 ሰው ግን ራሱን ይፈትን፥ እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤
29 ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና።
30 ስለዚህ በእናንተ ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ አያሌዎችም አንቀላፍተዋል።
31 ራሳችንን ብንመረምር ግን ባልተፈረደብንም ነበር፤
32 ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን።
33 ስለዚህ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ ለመብላት በተሰበሰባችሁ ጊዜ እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ።
34 ማንም የራበው ቢኖር ለፍርድ እንዳትሰበሰቡ በቤቱ ይብላ። የቀረውንም ነገር በመጣሁ ጊዜ እደነግጋለሁ።



ንባባት [፩ ቆሮ ፲፩፡ ፳፪ - ፴ ፣ ፩ጴጥ ፪፡ ፲፪-፳፭ ፣ ግ.ሓ. ፳፯፡ ፰ - ፴፫]

ምስባክ (መዝ ፳፪)
ወሠራዕከ ማእደ በቅድሜየ፡
በኣንጻሪሆሙ ለእለ ይሳቕዩኒ፡
ወኣጽሓድከ በቅብእ ርእስየ።
ሉቃስ ፳፪፡ ፩-፴
1 ፋሲካም የሚባለው የቂጣ በዓል ቀረበ።
2 የካህናት አለቆችና ጻፎችም እንዴት እንዲያጠፉት ይፈልጉ ነበር፤ ሕዝቡን ይፈሩ ነበርና።
3 ሰይጣንም ከአሥራ ሁለቱ ቍጥር አንዱ በነበረው የአስቆሮቱ በሚባለው በይሁዳ ገባ፤
4 ሄዶም እንዴት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ከካህናት አለቆችና ከመቅደስ አዛዦች ጋር ተነጋገረ።
5 እነርሱም ደስ አላቸው፥ ገንዘብም ሊሰጡት ተዋዋሉ።
6 እሺም አለ፥ ሕዝብም በሌለበት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ምቹ ጊዜ ይፈልግ ነበር።
7 ፋሲካንም ሊያርዱበት የሚገባው የቂጣ በዓል ደረሰ፤
8 ጴጥሮስንና ዮሐንስንም። ፋሲካን እንድንበላ ሄዳችሁ አዘጋጁልን ብሎ ላካቸው።
9 እነርሱም። ወዴት እናዘጋጅ ዘንድ ትወዳለህ? አሉት።
10 እርሱም አላቸው። እነሆ፥ ወደ ከተማ ስትገቡ ማድጋ ውኃ የተሸከመ ሰው ይገናኛችኋል፤ ወደ ሚገባበት ቤት ተከተሉት፤
11 ለባለቤቱም። መምህሩ። ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን የምበላበት የእንግዳ ቤት ክፍል ወዴት ነው? ይልሃል በሉት፤
12 ያም በደርብ ላይ ያለውን የተነጠፈ ታላቅ አዳራሽ ያሳያችኋል፤ በዚያም አሰናዱልን።
13 ሄደውም እንዳላቸው አገኙና ፋሲካን አሰናዱ።
14 ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
15 እርሱም። ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤
16 እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው።
17 ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት፤
18 እላችኋለሁና፥ የእግዚአብሔር መንግሥት እስክትመጣ ድረስ ከአሁን ጀምሮ ከወይኑ ፍሬ አልጠጣም አለ።
19 እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና። ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
20 እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው።
21 ነገር ግን አሳልፎ የሚሰጠኝ እጅ እነሆ በማዕድ ከእኔ ጋር ናት።
22 የሰው ልጅስ እንደ ተወሰነው ይሄዳል፥ ነገር ግን አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት።
23 ከእነርሱም ይህን ሊያደርግ ያለው ማን እንደ ሆነ እርስ በርሳቸው ይጠያየቁ ጀመር።
24 ደግሞም ማናቸውም ታላቅ ሆኖ እንዲቈጠር በመካከላቸው ክርክር ሆነ።
25 እንዲህም አላቸው። የአሕዛብ ነገሥታት ይገዙአቸዋል፥ በላያቸውም የሚሠለጥኑት ቸርነት አድራጊዎች ይባላሉ።
26 እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ፤ ነገር ግን ከእናንተ ታላቅ የሆነ በመካከላችሁ እንደ ታናሽ፥ የሚገዛም እንደሚያገለግል ይሁን።
27 በማዕድ የተቀመጠ ወይስ የሚያገለግል ማናቸው ታላቅ ነው? የተቀመጠው አይደለምን? እኔ ግን በመካከላችሁ እንደሚያገለግል ነኝ።
28 ነገር ግን እናንተ በፈተናዎቼ ከእኔ ጋር ጸንታችሁ የኖራችሁ ናችሁ፤
29 -30 አባቴ እኔን እንደ ሾመኝ እኔ ደግሞ በመንግሥቴ ከማዕዴ ትበሉና ትጠጡ ዘንድ፥ በአሥራ ሁለቱ በእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በዙፋኖች ትቀመጡ ዘንድ ለመንግሥት እሾማችኋለሁ።


Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 09 Apr 2026, 03:59

ዘሕፅበተ እግር (ዘ፱ቱ ሰዓት)

ንባባት [፩ ቆሮ ፲፩፡ ፳፫ - ፳፮ ፣ ፩ዮሓ ፭፡ ፭-፲ ፣ ግ.ሓ. ፳፮፡ ፴፫ - ፴፰]

ምስባክ (መዝ ፶)
ትነዝሓኒ በኣዛብ ወእነጽሕ፡
ተሓፅበኒ ወእምበረድ እጸዓዱ፡
ታሰምዐኒ ትፍሥሕተ ወሓሤት።
ዮሓ ፲፫፡ ፬ - ፲፮
4 ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤
5 በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።
6 ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም። ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው።
7 ኢየሱስም መልሶ። እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ አለው።
8 ጴጥሮስም። የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም አለው። ኢየሱስም። ካላጠብሁህ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም ብሎ መለሰለት።
9 ስምዖን ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው።
10 ኢየሱስም። የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሐን ናችሁ፥ ነገር ግን ሁላችሁ አይደላችሁም አለው።
11 አሳልፎ የሚሰጠውን ያውቅ ነበርና፤ ስለዚህ። ሁላችሁ ንጹሐን አይደላችሁም አለው።
12 እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው። ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?
13 እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ።
14 እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል።
15 እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና።
16 እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም።


ክብር ይእቲ ዛቲ ለኵሉ ጻድቃኑ፤ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ ለእግዚኣብሔር በቅዱሳኑ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በጽንዐ ኃይሉ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በክሂኢሎቱ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በከመ ብዝኅ ዕበዩ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በቃለ ቀርን ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በመዝሙር ወበመሰንቆ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በከበሮ ወበትፍሥሕት ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በኣውታር ወበእንዚራ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በጸናጽል ዘሠናይ ቃሉ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ሰብሑዎ በጸናጽል ወበ ይባቤ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ኩሉ ነፍስ ይሴብሖ ለእግዚኣብሔር ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ስብሓት ለኣብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

ለዓለም ወለዓለመ ዓለም ሃሌሉያ፡ ሓዋርያቲሁ ከበበ እግረ ኣርዳኢሁ ሓፀበ፡ ኮኖሙ ኣበ ወእመ ወመሀሮሙ ጥበበ ሃሌሉያ፡

በ፩ ሃሌሉያ፡ ሐፀበ እግረ አርዳኢሁ ወይቤሎሙ ኣነኒ ሐፀብኩ እገሪክሙ ኣንትሙኒ ከምዝ ግበሩ ለቢጽክሙ



Pope Francis kisses the foot of a refugee during Holy Thursday Mass of the Lord’s Supper at the Center for Asylum Seekers in Castelnuovo di Porto, north of Rome on 24 March. Photo: CNS photo/L’Osservatore Romano

Pope Francis blesses a baby during the foot-washing ritual at the Castelnuovo di Porto refugees center near Rome, Italy, on March 24, 2016. Osservatore Romano/Reuters
Pope Francis washes feet of Muslim refugees https://catholicweekly.com.au/pope-fran ... -refugees/



Pope Leo XIV washes and kisses the feet of 12 Roman priests during the Missa in Caena Domini, the Mass of the Lord’s Supper, on Catholic Holy Thursday in St. John Lateran Basilica in Rome, Thursday, April 2, 2026. (AP Photo/Andrew Medichini)

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 09 Apr 2026, 10:10

ዘዓርብ ስቅለት


ኣምንስቲት ሙኪርያ ኣንቲ ፋሲልያሱ
ኣምንስቲት ሙኣግያ ኣንቲ ፋሲልያሱ
ኣምንስቲት ሙድስቡጣ ኣንቲ ፋሲልያሱ


Image: Debre Berhan Selassie Church (Gondar, Ethiopia). Credit: iStock.com/MWayOut

ተዘከረኒ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ
ተዘከረኒ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ
ተዘከረኒ ኦ ኃያል በውስተ መንግሥትከ

Meleket
Member+
Posts: 5057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ዓቢይ ጾም + ጾመ 40 + ከአንዳንድ የቅዱስ መጸሐፍ መንፈሳዊ ሃሳቦች ጋር + 40 ጾም

Post by Meleket » 11 Apr 2026, 03:35

የመረጃ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በመላ፡

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ!

ዘመኑ የሰላምና የፍቅር የመተሳሰብና የመተባባር ዘመን ይሆንልን ዘንድ በክርስትያናዊ ፍቅር እያሳሰብን፡ አሁንም ደግመን ደጋግመን ትንሳኤው ትንሳኤያችንም ይሆን ዘንድ እንመኛለን!




Post Reply