የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ እናት የሆኑት ወይዘሮ አዳነች በርሄ፣ አንድ ምዕተ ዓመት (100 ዓመት) የሞላው የልደት በዓላቸውን እያከበሩ ይገኛሉ።
ልጃቸው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ለረዥም ዓመታት በበረሃ የትጥቅ ትግል ላይ በነበሩበት ወቅት፣ ቤተሰቡን በማስተዳደርና በመጽናት የሚታወቁ እናት ናቸው።
በኤርትራውያን ዘንድ፣ ከጣሊያን ቅኝ አገዛዝ ጀምሮ እስከ ዛሬዋ ኤርትራ ድረስ ያለውን ረዥም ታሪክ የተሻገሩ ሕያው መዝገብ ተደርገው ይወሰዳሉ።
በማሕበራዊ ሚዲያ አማካይነት ከተሰጡ አስተያየቶች መካከል፣ "አንድ ሰው መቶ ዓመት ሲኖር፣ መቶ ዓመት ሙሉ ታሪክን ተሸክሞ ይጓዛል" የሚል ይገኝበታል።
