Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

ቆምጬ

Post by Selam/ » 04 Mar 2026, 10:01

ገራገሩ ቆምጬ እንደምን ከርመሃል
ስትፀልይ ከልብህ ወፎች ይሰሙሃል
ፎጣም ልበስ ቁምጣ ሁሉም ያምርብሃል
ግርማና እርጋታህ መንፈስን ያረካል
የምቀኛን ቅስም ይሰብራል ይገድላል
ጮማም ብላ ጥሬ ፈገግታህ ያስቀናል
ለአናሳ ጎጠኞች ደም ፍላት ይሰጣል
ሲመሽም ሲነጋም ስምህን ያነሱታል

Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 04 Mar 2026, 18:41


Axumezana
Senior Member
Posts: 19006
Joined: 27 Jan 2020, 23:15

Re: ቆምጬ

Post by Axumezana » 04 Mar 2026, 19:12

ቆምጬ ታታሪ ነው አገር ይቀልባል
አአ አትግባ ቢሉት በርግዶ ይገባል
አገር ነፃ አውጥቶ ፍትህን ያነግሳል
ናቂ ውዳቂ ነው ተቀምጦ ያገሳል
Last edited by Axumezana on 04 Mar 2026, 19:13, edited 1 time in total.

Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 04 Mar 2026, 19:13




Misraq
Senior Member
Posts: 17405
Joined: 27 Sep 2009, 19:43
Location: Zemunda

Re: ቆምጬ

Post by Misraq » 04 Mar 2026, 19:26

ቆምጬ ገራገሩ ያገር ጠባቂው
ረሃብ ቸነፈር ግፍ ያልበገረው
ቂምን የማይቋጥር መቻቻል ባህሉ
አግብቶ ተጋብቶ በሃገሩ ሁሉ
ሕዝብን አንድ አድርጎ በድንቅ ባህሉ
ይኖረው ነበረ በሃገሩ ሁሉ

Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 04 Mar 2026, 19:44

ደጉ ገራገሩ ፣ ቆምጬ ባላገሩ
ቢያጣ ቢገረጣ ፣ ፈገግታው ማማሩ
ዕኩል ሁሉን የሚያይ ፣ ስብዕናው ኩሩ
ጎጠኛ ሲንጫጫ ፣ ሲያፍር በሃገሩ
ባለ ቁምጣው ጎበዝ ፣ ጅንን ስመ ጥሩ




Last edited by Selam/ on 04 Mar 2026, 19:55, edited 1 time in total.

Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 04 Mar 2026, 19:52


Meleket
Member
Posts: 4954
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ቆምጬ

Post by Meleket » 05 Mar 2026, 03:30

በምድር እያለ በሰማይ ላይ ኗሪ፡
በምድር እያለ እንደሰማይ ኗሪ፡
አምላክና ሰውን ሁሉንም አክባሪ፡
ንጹህና ቅዱስ ሃብቱ ለፈጣሪ፡
ቆምጬ እንደሆነ እኛ ነን መስካሪ።

ተጻፈ በኛ በኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በተለመደው ኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር።

Selam/ wrote:
04 Mar 2026, 19:13



Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 05 Mar 2026, 09:55

ቆምጬ በቀደሰው ባርኮ በመረቀው
ሳይማር በልቡ ፈጣሪን ባመነው
ጎጠኛ ዕንቅልፍ አጣ ጨነቀው ጠበበው



Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 06 Mar 2026, 09:15

ሺ ተንኮል ቢያስቡ ፣ ጎጠኞች ቢያሴሩ
ከተፈጥሮ ፀጋው ፣ ሊያወርዱት ቢጥሩ
ቆምጬው ባላገሩ ፣ በሃገሩ ኩሩ
ሁሉን ሰው አክባሪ ፣ ትህትናው ጥሩ

Meleket
Member
Posts: 4954
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ቆምጬ

Post by Meleket » 06 Mar 2026, 09:41

“ቆምጬ ቆምጬ” እያሉ ሊያጥላሉት ሞከሩ፡
እነ አውርቶ-አደር፡ እነ ስራ አይሰሩ!
ምላሳቸው ረዝሞ እነ ቆርጦ ቀጥል፡
ቆምጬን ቢያጥላሉትም ሆኖባቸው አመል፡
እሱ ግን፡ ምን ግዱ፡ ቀንበር ተሸክሞ፡
ለከተሜው ምቾት ገጠር ላይ ከትሞ፡
ደማቁን ፈገግታ ከአምላክ ተሸልሞ፡
አርሶ-አጭዶ አበላቸው አሁንም ደጋግሞ።

ተጻፈ በኛ በኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በተለመደው ኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር።

Selam/ wrote:
04 Mar 2026, 19:52

Dama
Member+
Posts: 7415
Joined: 22 Jun 2024, 21:05

Re: ቆምጬ

Post by Dama » 06 Mar 2026, 10:39

Each of you above carry lots of pain inflicted by each of you against each other. Pains engraved on loss of lands one to the other. In addition, Human remains killed by each other remain unburried and strewn across plains, valleys and mountains.
Regardless, you came together to rehabilitate a character destroyed for good reasons by Odie from Gurage.

I got your notice that despite your grave losses to each other, you would gang up against Gurage when it fights Amara oppression. That Gurage to each of you is an alien enemy clearly proving your racism and xenophobia. That you would oppress and dehumanize Gurage together.
Last edited by Dama on 06 Mar 2026, 10:53, edited 1 time in total.

Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 06 Mar 2026, 10:44

የህዝቦቼ አንድነት ፣ ዕንቅልፍ የነሳቸው
ኢትዮጵያን ማናከስ ፣ ያረጉ ዓላማቸው
የጥላቻ ወባ ፣ ያርገፈገፋቸው
ቆምጭዬን ከማማው ፣ ሊያወርዱ አማራቸው
መቋጠሪያው ውሉ ፣ መሆኑ ጠፍቷቸው

Dama
Member+
Posts: 7415
Joined: 22 Jun 2024, 21:05

Re: ቆምጬ

Post by Dama » 06 Mar 2026, 10:55

Selam/ wrote:
06 Mar 2026, 10:44
የህዝቦቼ አንድነት ፣ ዕንቅልፍ የነሳቸው
ኢትዮጵያን ማናከስ ፣ ያረጉ ዓላማቸው
የጥላቻ ወባ ፣ ያርገፈገፋቸው
ቆምጭዬን ከማማው ፣ ሊያወርዱ አማራቸው
መቋጠሪያው ውሉ ፣ መሆኑ ጠፍቷቸው
Zerenga $hrmuta. You can also summon your donkeys.

Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 06 Mar 2026, 10:55

ቆምጭዬ ቤተኛ ፣ ትግሬ ጎረቤቴ
ጉራጌው አጎቴ ፣ ኦሮሞው አማቴ
ኤርትራ እንግዳዬ ፣ ይቀመጥ ከፎቴ
ተቃጠል ጎጠኛ ፣ ዕለቅ በሸርታቴ

Dama
Member+
Posts: 7415
Joined: 22 Jun 2024, 21:05

Re: ቆምጬ

Post by Dama » 06 Mar 2026, 12:21

Selam/ wrote:
06 Mar 2026, 10:55
ቆምጭዬ ቤተኛ ፣ ትግሬ ጎረቤቴ
ጉራጌው አጎቴ ፣ ኦሮሞው አማቴ
ኤርትራ እንግዳዬ ፣ ይቀመጥ ከፎቴ
ተቃጠል ጎጠኛ ፣ ዕለቅ በሸርታቴ
You thugs represent no one. You are hateful. Ypu are racists. Ordinary Amara is not hateful, not racist. You do not speak the language of the people. You do not represent them. Ypu spew hate of your own making.
Std P*mps!!

Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 06 Mar 2026, 13:22

ቆምጬ ገራገሩ ፣ ሁሌ ልበ ሙሉ
ቢሰድቡት ቢጎዱት ፣ ሸጋ ነው አመሉ
የሚጠሉት ጉጦች ፣ ወረዱ ቀለሉ
ለምህረት ለመኑት ፣ እየተከተሉ

Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 06 Mar 2026, 13:45




Selam/
Senior Member
Posts: 17336
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ቆምጬ

Post by Selam/ » 06 Mar 2026, 14:05

ቆምጬው እረኛዬ ፣ ትንሹ ጌታዬ
ከአውሬዎች አዳነኝ ፣ ነፍሴን ጠባቂዬ



Meleket
Member
Posts: 4954
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ቆምጬ

Post by Meleket » 07 Mar 2026, 04:01

ጉራጌን ታማራ ሊያናክስ አስቦ፡
ትግራይን ታማራ ሊያቧጭቅ አስቦ፡
አገውን ታማራ ሊያቃቅር አስቦ፡
አንዱን ጎሳ ታንዱ ሊያናቁር አስቦ፡
ካድሬው ብልጥግና መጣ አላማ አንግቦ፡
የ‘ኢ-ዜማው' ካድሬ መጣ አላማ አንግቦ፡
ግርማም ወደብ አለ እንዲያው ተስገብግቦ፡
እንዲያ ታላረገ ስለማይኖር ጠግቦ!

በሁለት ቀን ልዩነት፡
አንዱ ‘ጁን’ 22፡
አንዱ ‘ጁን’ 24፡
ተከታትሎ መጥቶ መረጃን በከላት።

ህዝብ እንደማፋቀር፡
ሲሰጥህ ዓላማ ህዝብን ለማናቆር፡
ትግተለተላለህ፡ ኣዬ “የካድሬ” ነገር!

‘ታትዬና ኣብዬ’ ሁለቱ እያዩን፡
‘ክልላነ’ ልንል ይህን የሰው ብኩን፡
ቆምጬን እንዳይነካብን ልንነግረው ቁርጡን!
እንግዲህ ተባብረን ‘ጨቁነናል ስልኩን!’

ለመዝናናትም ጭምር፡ ተጻፈ በእኛ በኤርትርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በተለመደው ኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና !

Selam/ wrote:
06 Mar 2026, 13:45



Post Reply