Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum









MINILIK SALSAWI
Senior Member
Posts: 11059
Joined: 24 Aug 2012, 12:02
Contact:

Re: ዘመቻ አንድነት በመላው አማራ

Post by MINILIK SALSAWI » 28 Aug 2025, 02:30

እውነተኛ የአማራ ፋኖ አንድነት የሚመጣው ከፋኖ ሰራዊታችን እስከ ከፍተኛ አመራሩ አምኖባቸውና ተከትሏቸው፣ ከፊት የተሰየሙትን የአማራ ፋኖ በጎጃም ፊታውራሪዎችን “መሪዎቻችን ናቸው” ብሎ ከመቀበል ይጀምራል። መሪዎቻችን ላይ የሚደረግ የገፅታ ገደላን በዝምታ እያለፉ፤ በመሪዎች ላይ የተደረገውን “የትግሉን አትመሩም” ሂደትን ይሁንታ እየሰጡ ‘አንድነትን መስበክ’ አይናችሁን ጨፍኑና ላሞኛችሁ አካሄድ መሆኑንም እንረዳለን። ባለፉት ፪ዓመት የአፋጎ ወታደራዊ መምሪያ ለአማራ ፋኖ ድርጅቶች አንድነት መሳካት የከፈለው ዋጋና የተወጣው ሚና በገሀድ እየታወቀ በትግሉም ሆነ ሰንሰለቱ ውስጥ ከዚህ ግባ የሚባል ሚና የሌላቸው አካላት “የድህረ ስልጣን ማደላደያ መንገድ ለማመቻቸትና ርካሽ ተወዳጅነት ለማግኘት” ሲባል ማኅበራዊ ገፃቸው ላይ ወጥተው የሚሞነጭሩት ፅሁፍ ፍፁም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እንድትገነዘቡ እንገልፃለን። በድርጅታችን ደንብና መመሪያ መሰረትም ለውስጥ አንድነታችን መሻከር በር የሚከፍቱትን ሁሉ ተጠያቂ እንደሚሆኑ እየገለፅን ትኩረታችን ሁሉ ደመኛ ጠላታችን ከሆነው የአብይ አህመድ ሰራዊት ላይ እንዲሆን ስንል እናሳስባለን። ..... ቀድሞውንም ነገር ጠላት ጋር ከተሳሰረ ውሎ ያደረ ጋብቻ እንዳለ ግልፅ ነው። ይህ ሂደት ከፊት የቀደሙንን ወንድሞቻችንን ለማስታወስና በእነሱ መንፈስ ጠላትን ልናሽመደምድበት እጅጉን ከተዘጋጀንበት "ዘመቻ ሰማዕታት" ጋር መገጣጠሙ ደግሞ ነገሮችን በአንክሮ ለመከታተል ተገደናል። ( ከአማራ ፋኖ በጎጃም ወታደራዊ መምሪያ የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ የተወሰደ )











Post Reply