Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 39869
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

ሞላ ማሩ!

Post by Horus » 02 Aug 2025, 17:14

ጊቢሶ ገበያ ማለት ከአማውቴ በላይ በአዲስ አበባ መንገድ ያለ ትልቅ የቅዳሜ ገበያ ነው! ብዙ ብዙ ግዜ ከናቴ ጋር ሂጄበታለሁ ! ( የሶዶ ጉራጌዎችና የበቾ ኦሮሞች መገበያያ የነበረ)።
ኦጀ ማለት ከብት መጠበቂያ (መገጃ) ደቦ ማለት ነው። እኔ ኦጀ ጥብቂያለሉ ፤ ማለትም ጠዋት ሁሉም ከብቱን አውጥቶ የኦጀ ተራ ለደረሰበት ልጅ ያስረክባል ።ያ ልጅ ከብቶቹን ሲጠብቅ ውሎ ማታ ለየቤቱ ያስረክባል ። በማግስቱ ሌላ ልጅ ተመሳሳይ ያረጋል ... ይህ ኦጀ ነው ፤ ሴቶች እንሰት የሚፍቁበት ደቦ ዉሳቻ ይባላል ። ወንዶች እንሰት የቆፍሩበት ደቦ ድድቅ ይባላል ። እርሻ የሚታረስበት ወይም እህል የሚታጨድበት ደቦ ይባላል። ሰርግ ካለ የጌሾ መውቀጫ ደቦ ውዘተ ወዘተ አለ ። ይህ የጉራጌ ሴራ ነው!!!