Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Za-Ilmaknun
- Member
- Posts: 4486
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40
Post
by Za-Ilmaknun » 06 Jan 2025, 13:59

ጥቂት የኦሮሞ ፖለቲከኞች ሕገ መንግሥቱን በመፃረር በአንድ በኩል ፌዴራላዊ ሥርዓት እንዲያብብና የብሔር ብሔረሰቦች መብት እንዲከበር እንፈልጋለን በማለት የፌዴራላዊ ሥርዓት አቀንቃኝ ሆነው ለመታየት ሲከጅሉ፣ በሌላው መልካቸው ደግሞ ሌላ አናሳና ነባር ሕዝቦችን የራስ በራስ የማስተዳደር ኅብረ ብሔራዊነትን በመደፍጠጥ የአንድ ብሔር የበላይነት በመገንባት ፀረ ሕገ መንግሥትታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ለበርካታ ዓመታት በኦሮሞና በሐረሪ የነበረውን የጋብቻ፣ የባህል፣ የሃይማኖት፣ የሥነ ልቦና አንድነት በመበጣጠስ ሁከትና ጥላቻ በሕዝቦች መካከል አለመተማመን እንዲኖር ፀረ ሰላም በሆነ መንገድ ለመንቀሳቀስ ሲሞክሩ ይስተዋላል፡፡
ነገር ግን መሆን የነበረበት ሌሎቹን በመደገፍ አብሮ በመሥራትና አብሮ በአንድነት፣ በፖለቲካና በኢኮኖሚ በመተሳሰር የአገርንና የሕዝቦችን ችግር በመቅረፍ የበለጠ የተረጋጋ ማኅበረሰብ በመፍጠር የአገራችንን የሁከት ፖለቲካ መለወጥ በተቻለ ነበር። ሐረሪዎችና የሐረሪ ክልል ሌሎቹን አቅፈው ፍቅር በመለገስ ሐረሪዎች ሐረርን በሥልጣኔ በዓለም ቅርስ እንዳስመዘገቡት፣ የኦሮሞ የዘውግ ፖለቲከኞች ክልሎችን ለሌሎች ፍቅር መለገስና ሁሉን ዜጋ አቃፊ መሆን መልካምነት ሲሆን፣ በተቃራኒው የሌሎችን ሀብትና መሬት በሕገወጥነት መውረር መደፍጠጥና ማፈናቀል ክልሎችን መሰረዝና መደለዝ ታላቅ ሕገ መንግሥታዊ ጥሰትና ወንጀል ነው። ሰሞኑን ታኅሳስ 13 ቀን 2017 ዓ.ም. በእነ አቶ ብርሃኑ ቦሬሳ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ቀረበ በተባለው አጀንዳ ሐረር ከተማ በኦሮሚያ ይጠቃለል ብለዋል፡፡
https://www.ethiopianreporter.com/137056/
-
Dama
- Member+
- Posts: 6416
- Joined: 22 Jun 2024, 21:05
Post
by Dama » 06 Jan 2025, 18:32
Ethnic groups of Harari region
Oromo (56.41%)
Amhara (22.77%)
Harari (8.65%)
Gurage (4.34%)
Somali (3.87%)
Tigray (1.53%)
Argobba (1.26%)
Other (1.17%)
Based on the 2007 Census conducted by the Central Statistical Agency of Ethiopia (CSA), Harari has a total population of 183, 415.
https://en.m.wikipedia.org/wiki/Harari_Region
Similar situations exist in the Mareq and Kebena weredas of Gurage. Majority of populations in each of the weredas are Gurages but they are included in the weredas despite their public protests where they have no civic rights to public office, public service discriminations, etc.
A Gurage opposition party calls for gov interventions.
https://addisstandard.com/gurage-opposi ... -violence/