Please wait, video is loading...
መከላከያ ብሄር የለውም ይልህና ብሄር ለይቶ ደግሞ ያስርሃል ምን ማለት ነው?"
የትግራይ ተወላጅ አሁን በመከላከያ ሰራዊት በ84ኛ ክ/ጦር ውስጥ ያለው ኮነሬል ሃፍቶም በአንድ ወቅት በስብሰባ የተናገረው መልእክት ነበር።
ከዚህ በታች ያለው ከቃለ መጠየቁ የተወሰዱ የትግርኛው ትርጉም ነው።
ፋኖ ሰለሞን ወልደገሪማ፦ የምትመለከትዋቸው ከአገዛዙ ሰራዊት የመጡ ወንድሞቻችን ናቸው።
ከመሃከላቸው የትግራይ ተወላጆችም አሉ ፤ ከዚህ በፊትም ብዙ የትግራይ ተወላጆች ወደኛ ወደ ፋኖ መጥተው ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝቷል።
ወደ ጥያቄው ሲገባ አምሳለቃ እስኪ የመጣህበት ክ/ጦርና የነበረህ የስራ ድርሻ አንስተህ ስሜትህ አጋራን?
አምሳለቃ፦ አምሳለቃ ፀሃየ ብርሃኑ እባላለሁ የመጣሁበት ከ84ኛ ክ/ጦር ስሆን የሻበል መሪ ነበርኩ።
አምሳለቃ ይቀጥላል .... ከዚህ በፊት የትግራይ ተወላጅ በመሆኔ ብቻ ሁለት አመት ከሰባት ወራት በእስር ቤት ነበርኩ ፤ ወደ ሃላፍነት ያመጡኝ አንድም ሰው ስላጡ ሁለተኛም በሽመት ለማታለል እንጂ እኔን ፈልገው አይደለም ያወጡኝ።
ፋኖ ሰለሞን ወልደገሪማ፦ ከዚህ በፊት የትግራይ ተወላጆች የመከላከያ አባላት ተለይተው ታሰሩ ዛሬ የአማራ ተወላጆች ሲታሰሩ እናንተ ደግሞ አማራን ለመጨፍጨፍ ተጠራቹ እና ይህ ምን ማለት እንደሆነ የአብዪ ሴራ ተገንዝባቹ በወገናቹ ላይ ባለመተኮስ ወደ ፋኖ እንድትቀላቀሉ የሚል ጥሪ አድርገን ነበር ጥሪው ሰምታቹት ነበር? ከሰማቹትስ ምን ተሰማቹ?
አምሳለቃ፦ አዎ ሰምተነዋል ከታችኛው እስከ ላይኛው አመራር ሰምቶታል ፤ በጎንደር ጎጃም እኛ ባለንበት በሸዋ ሳይቀር ሁሉም ሰምቶታል።
እውነት ነው ትላንት እኛ ተጋሩ አሰረን ዛሬ አማራ እየታሰረ ነው አሁን የተጋበዝነው የአማራ ህዝብ እንድንጨፈጭፍ ነው እኛ ግን በጭራሽ አናረገውም ለዚህ ነው ወደ ፋኖ ወደን እየገባን ያለነው። አሁን ከፋኖ ጎን ሆኜ መታገል ወይም ወደቤተሰብ ለመሄድ ነው ፍላጎቴ።
ለማንኛው የሰጠሁህ ስልክ የከፍተኛ አመራር የትግራይ ተወላጆች ፍላጎት ስላላቸው አነጋግራቸው።
ፋኖ ሰለሞን ወልደገሪማ፦ አመራሮቹ እያገኘናቸው እንገኛለን የገቡም አሉ በቅርብ በብዛት እሚቀላቀሉንም ይኖራሉ በተመሳሳይ ለትግራይ ተወላጆች የማታለያ ሽመት እየሰጠ ነው ወደ ግንባር እያመጣቹ ያለው የሚባለው ምን ያህል እውነት ነው?
አምሳለቃ፦ እውነት ነው ከእስር እንደፈታን ወደ ተሃድሶ ወሰደን ስንብት ስንጠብቅ የመደለያ ሽመት እየሰጠ ወደ ግንባር አመጣን።ግን በቅርብ ታየዋለህ ጦሩ ይፈርሳል።
በነገራችን ላይ ለመከላከያ ሰራዊት የሚነገረው ፋኖ ገዳይ እንደሆነ ነው እኔ ግን በአይነ አይቸዋለሁ ህብረተሰቡ ከህፃን ጀምሮ እስካዋቂ የስርዓት እንጂ የብሄር ጥላቻ የለውም ለወደገብ መከላከያ ከፍተኛ አቀባበልና እንክብካቤ ነው የሚያደርገው። እውነት ለመናገር በተለይ ለሌላ ብሄር ያለው እንክብካቤ ከገዛ ልጆቹ በላይ ነውና ለመከላከያ አባላት የትግራይ ተወላጆች ወደ ፋኖ እንዲቀላቀሉ ጥርዬን አቀርባለሁ።
ሙሉ ዝርዝሩ ከAnchor Media ይመልከቱ።