Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4486
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

በደቡብ ኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ክፍያ መቅረት እና ያስከተለው ቀውስ

Post by Za-Ilmaknun » 03 Sep 2024, 11:20

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ውስጥ በሚገኙ 21 ወረዳዎች ተቀጥረው በማገልገል ላይ የነበሩ የመንግሥት ሠራተኞች የወር ደሞዛቸው ለረዥም ጊዜ በመቁረጡ ለኢኮኖሚያዊ እና ማሕበራዊ ችግሮች ተጋለጣቸውን አስረድተዋል::ወላይታ ዞን የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ስለማይከፈላቸው አንዳንድ መምህራን የተማሩባቸውና ሲያገለግሉበት የነበረውን ሞያ ትተው በግብርና ሥራ መሰማራታቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ::

በዳሞት ወይዴ ወረዳ ብቻ ከ3ሺህ በላይ ሠራተኞች ለወራት ደመወዛቸው ባለመከፈሉ ቤተሰቦቻቸውን ማስተዳደር እንደተሳናቸውና ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን ዘርዝረዋል::

ከደሞዝ አለመከፈል ጋር በተያያዘ በዳሞት ወይዴ ወረዳ ያሉ አራት ጤና ጣቢያዎች እና አንድ ሆስፒታል በመሉ አቅሙ አገልግሎቶችን እየሰጡ አለመኾናቸው እና በዚህም የተነሳ የአከባቢው ማህበረሰብ የጤና እና ትምህርት አገልግሎቶችን የማግኘት መብት መጣሱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በትላትናው ዕለት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል::

https://amharic.voanews.com/a/7768782.html

sesame
Member+
Posts: 7968
Joined: 28 Feb 2013, 17:55

Re: በደቡብ ኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ክፍያ መቅረት እና ያስከተለው ቀውስ

Post by sesame » 03 Sep 2024, 13:21

Abiy is more interested in building a $10 Billion palace and corridors in Addis! He can't be bothered about paying wages to his poor people!

Post Reply