Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4486
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ዋልጋና ዳርጌ ከተሞች የተከሰተው

Post by Za-Ilmaknun » 06 Aug 2024, 12:26

ትናንትናው እለት ወደ ስፍራው የገቡ በርካታ የመንግስት ሀይሎች ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ የቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ በዛ ያሉ የአካባቢውን ወጣቶች እና ባለሀብቶች በቁጥጥር ስር እንዳዋሉ ከስፍራው ለመሰረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።

“ኮማንዶ ፌደራል ፖሊስና የተለያዩ ከባድ መሳሪያዎችን የያዙ የመንግስት ሀይሎች ዛሬ ከጠዋት 11:30 ጀምረው ባለሀብቶች እና ወጣቶችን ፋኖን ታደራጃላችሁ በማለት ሲያፍሱና በኦራል ሲጭኑ ውለዋል” ብለው መረጃ ያደረሱን አንድ የአካባቢው ነዋሪ ናቸው።

ሌላ መረጃ ሰጪ ደግሞ ድርጊቱ መፈፀሙን ጠቁሞ አሁን ከ70 በላይ ሰዎች ለእስር እንደተዳረጉ እና “የጦር መሳሪያ አላችሁ” በሚል የመሳርያ ለቀማ ተከናውኗል ብለዋል።

“ከተሞቹ በአሁን ሰአት ምንም የሚንቀሳቀስ ሰው የለም፣ ማህበረሰቡም ተረብሿል” ያሉት የመሰረት ሚድያ የመረጃ ምንጮች ወረዳው በብዛት የአማራ ብሔር ተወላጆች የሚኖሩበት እንደሆነ ጠቁመዋል።

-መሰረት ሚድያ-

Dama
Member+
Posts: 6461
Joined: 22 Jun 2024, 21:05

Re: በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ዋልጋና ዳርጌ ከተሞች የተከሰተው

Post by Dama » 06 Aug 2024, 12:52

Abiy try your best. You know you are just buying time by your draconian measures.

Post Reply