Please wait, video is loading...
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: በአማራ ክልል ከሕግ ውጪ ግድያ እንዲቆም እና ፈጻሚዎች ለሕግ እንዲቀርቡ አምነስቲ ጠየቀ
26 የካቲት 2024
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በአማራ ክልል እየተካሄደ ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ከሕግ ውጪ ይፈጽማል ያለውን ግድያ እንዲያቆም እና በድርጊቱ የተሳተፉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጠየቀ።
አምነስቲ ዛሬ ባወጣው አጭር ሪፖርት ላይ በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባሕር ዳር በሰላማዊ ሰዎች ላይ ተፈጸሙ ያላቸውን እና መረጃ ያሰባሰበባቸውን ግድያዎችን በመጥቀስ የደረሱ ጉዳቶችን አቅርቧል።
በተለይ በግጭቱ የመጀመሪያ ወራት በባሕር ዳር እና አካባቢዋ በመከላከያ ሠራዊት ከሕግ ውጪ ግድያዎች መፈጸማቸውን የጠቀሰው አምነስቲ፣ በአንዳንድ ሁኔታዎች “ቤተሰቦች የሟቾችን አስከሬን በማንሳት እንዳይቀብሩ” እንደተከለከሉ በሪፖርቱ ላይ ገልጿል።
በሪፖርቱ ላይ የመከላከያ አባላት ባለፈው ዓመት ነሐሴ ላይ ቀበሌ 08 በተባለው አካባቢ አቡነ ሃራ እና ልደታ በተባሉ ሰፈሮች በስድስት ሰዎች ላይ የፈጸሟቸውን ከሕግ ውጪ የሆኑ ግድያዎችን መዝግቧል። በተጨማሪም በጥምት ወር መጀመሪያ ላይ ሰባታሚት በተባለ ስፍራ ሌሎች ስድስት ሰዎችን መግደላቸውን አመልክቷል።
በአማራ ክልል በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተካሄደ ባለው እና ወራትን ባስቆጠረው ግጭት ምክንያት ሰላማዊ ሰዎች ሰለባ መሆናቸውን ያመለከተው አምነስቲ፣ አስተማማኝ መረጃ ለማግኘት እንቅፋቶች እንዳሉም ጠቁሟል።
ግጭቱ በሰብአዊ መብቶች ላይ ያሳደረገውን ተጽእኖ ለመረዳት በመገናኛ ዘዴዎች መቋረጥ እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የመናገር እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ነጻነት ላይ ጫና በመፍጠር እና የበቀል እርምጃን መፍራት መረጃዎች በአዝጋሚ ሁኔታ እንዲወጡ እያደረገ ነው ብሏል።
አምነስቲ የአፍሪካ ቀንድ ተጠሪው ሱዑድ ኑር እንዳሉት የኢንተርኔት መቋረጥ ባለበት ሁኔታ ከርቀት ምርመራ ማካሄድ ከፍ ያለ ጥንቃቄን የሚሻ መሆኑን አመልክተው፣ ነገር ግን “በክልሉ እና በአገሪቱ ውስጥ ከሚካሄዱ ወታደራዊ ግጭቶች ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ የመብት ጥሰቶችን መከታተላችንን እንቀጥላል” ብለዋል።
አምነስቲ ባሰባሰበው መረጃ መሠረት ከሕግ ውጪ የሚፈጸሙት ግድያዎች የሰዎችን በሕይወት የመኖር መብት ጥሰት እና ከባድ ዓለም አቀፍ የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶች መፈጸማቸቀውን እንደሚያመለክቱ በመግለጽ፣ እነዚህም በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ከጦር ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ ሊሆኑ ይችላሉ ብሏል።
የመብት ተቆርቋሪው ድርጅት በኢትዮጵያ የእንዲህ ዓይነት ወንጀል ፈጻሚዎችን ተአማኒ በሆነ የፍትህ ሥርዓት ተጠያቂ ባለመሆናቸው ተደጋግመው እንዲፈጸሙ ምክንያት መሆኑን ጠቅሶ፣ “በመላው አገሪቱ የሚታየውን የፍትህ መጓደል እንዲያበቃ እና ተጠቃቂነት እንዲሰፍን” ጥሪ አቅርቧል።
አምነስቲ ባለፈው ዓመት ነሐሴ እና በዚህ ዓመት ጥቅምት ወር ባሕር ዳር ውስጥ በመንግሥት ኃይሎች የተገደሉትን ሰዎች ቤተሰቦች እና የዐይን እማኞችን በማነጋገር ምስክርታቸውን በሪፖርቱ ውስጥ አካቷል።
በወታደሮች ግድያዎች ከተፈጸመ በኋላ ቤተሰቦች የሟቾችን አስከሬን እንዳያነሱ መከልከላቸውን እና ወታደሮቹ ከአካባቢው አስኪሄዱ ለረጅም ሰዓታት መጠበቅ እንደነበረባቸው እንዲሁም በተፈጠረባቸው ስጋት ሟቾችን በድብቅ ለመቅበር መገደዳቸውን ተናግረዋል ብሏል።
“መንግሥት በክልሉ ውስጥ እየተካሄደ ካለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ ምርመራ በአስቸኳይ እንዲጀመር እና ድርጊቱን በመፈጸም በቂ ማስረጃ በተገኘባቸው ላይም ዓለም አቀፍ ደረጃን በጠበቀ ሁኔታ በሕግ እንዲጠየቁ” ሲሉ የአምነስቲ የምሥራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ዳይሬክተር ቲጌሬ ቻጉታህ ጥሪ አቅርበዋል።
ምስክርነታቸውን ለአምነስቲ የሰጡት ግለሰቦች ግድያዎቹ በመከላከያ ሠራዊት አባላት መፈጸማቸውን እንዴት እንዳወቁ ተጠይቀው፣ አብዛኞቹ የሠራዊቱ አባላት ለወራት በባሕር ዳር ሲንቀሳቀሱ ስለነበር በደንብ ልብሳቸው እንደሚለይዋቸው ተናግረዋል። አንዳንዶች ደግሞ “የጦር መሳሪያ አምጡ፤ ፋኖን ትደግፋላችሁ?” በሚል የሟቾችን ቤተሰቦች መጠየቃቸውን ገልጸዋል።
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44