Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Horus » 17 Dec 2023, 02:11

ትግሬ + 0 = ትግሬ አልቻለም
ኦሮሞ + 0 = ኦሮሞ አልቻለም
አማራ + 0 = አማራ አልቻለም
ኦሮሞ + አማራ = ኦሮማራ አልቻለም
ኦሮሞ + ትግሬ = ትግኦሮ አይችልም
አማራ + ትግሬ =አማትግ አይችልም
ኦሮሞ + አማራ + ትግሬ =ኦሮማራትግ አይችልም
ከዛሬ እስከ አለም ፍጻሜ አንድ ጎሳ ያሻውን ያክል ቢገነታ የኢትዮጵያን እድል አይወስንም፣ አይቆጣጠርም
ያሻቸውን ያክል ጎሳዎች ቢደመሩ የኢትዮጵያን እድል አይወስኑም
የማንኛውም የጎሳ በላይነት ሂሳብ ተቃራኒ አፍራሽ የጎሳ ቀመር ይሰራለታል
ይህ ተረት አይደለም! ይህ ምኞት አይደለም
ሳይንስ ነው !

ሆረስ ነኝ


Naga Tuma
Member+
Posts: 5944
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Naga Tuma » 18 Dec 2023, 02:13

የጻፍካቸዉ ፎርሙላዎች ሁሉ ዉስጥ ጉራግኛ ተናጋሪ ስለሌለ ነዉ የማይሰራዉ። ለጫወታ ነዉ።

በቁም ነገር ሰሞኑን ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ይለምለም እያልኩ ሰነበትኩኝ።

ኢትዮጵያ ዉስጥ ሳይንሳዊ አስተሳሰንብ ከፍ ማድረግ እንጂ ዝቅ ማድረግ ኣይቻልም።
Last edited by Naga Tuma on 18 Dec 2023, 09:18, edited 1 time in total.

Misraq
Senior Member
Posts: 14358
Joined: 27 Sep 2009, 19:43
Location: Zemunda

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Misraq » 18 Dec 2023, 02:26

መፍትሔው ታድያ ምንድን ነው? ብርሃኑ ነጋ ይምራ ነው?

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Horus » 18 Dec 2023, 02:47

ናጋ ቱማና ምስራቅ ፣ ለምን ስዩም ተሾመን አታማክሩትም ! እሱ አይደል እንዴ የኦሮማራና ትግኦሮ ፈልሳፊ ? ፈስ ያለበት ዝላይ አይችልም :lol: :lol: :lol:

Fiyameta
Senior Member
Posts: 15768
Joined: 02 Aug 2018, 22:59

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Fiyameta » 18 Dec 2023, 07:12

Empires formed by conquest have always fallen on their own swords. Ethiopia's failure to transition from a medieval empire to modern nation-state has complicated its path towards national unity, as every group that ascended to power over its 100 years of history has defined itself based on its own ethnic identity, and pledged allegiance to its power base, as opposed to the nation.

It gets even more complicated if the ruling party hails from a tiny ethnic minority that it has no choice but to make itself subservient to powerful nations in order to lord over the majority. But what we are seeing today is that, even when an ethnic majority ascends to power, since the country still remains a medieval empire, it cannot escape the subservience culture that was preserved, nurtured and instituted by its predecessors for a millennia.

Admitting mistakes can be very painful for your ego, as it is only natural for people to deny facts in order to protect their self-image. But admitting flaws and acknowledging past mistakes tends to unify a nation in a way nothing else does. The Truth and Reconciliation Commission established in South Africa, for example, to a certain extent has helped the country transition from an Apartheid state to a Nation-State.

Abere
Senior Member
Posts: 12913
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Abere » 18 Dec 2023, 10:00

The only time in the history of Ethiopia an ethnic group become political leader is in the era of Tigre-Woyane and Oromo-OLF. And there has never been such a thing even in the history of mankind. The very reason Ethiopia has been among the few oldest nation and an only country of symbol of independence in the world is because Ethiopians are unified as citizens with strong love of their country. Ethnic politics is the booby-trap set against the existence of this ancient country known as Ethiopia by her historical enemies and mercenaries. Everyone knows including our enemies and their trolls. But they are trying their arse off to confound reality and confuse us.

Yes, it is Universal Truth ethnicity can neither be a political ideology nor a leadership. Ethnic politics only gives generous opportunity to enemies of Ethiopia to feast over her. Our enemies are working hard preying on turning Ethiopia into their political carcass so as to create anarchy in horn of Africa - where all types of wild beasts have their water point. As everything in under the universe has an end the Tigre-Woyane and Oromo-OLF/PP has already hit a dead-end road. The fact that the Woyane and OLF tribal empire collapsed and totaled, has made the enemies of Ethiopia, far and near, frantic nervous. However, none of them can resuscitate and breath life into it. It is dying effectively fact that the Amhara Fano aggrandize mass support and its call revibrating around is a testimony of the dawn of freedom and the renaissance of Ethiopia - making her historic enemies crazy fumbling deal this negotiation that to stop the hurricane bulldozing the ethnic aparthied wall built by our enemies.. :mrgreen:

Congratulations to Ethiopians, the tribal booby-trap homework imposed upon Ethiopians is collapsing. Fano is demolishing it. Let it be also clear, there will not be gain without pain.

Misraq
Senior Member
Posts: 14358
Joined: 27 Sep 2009, 19:43
Location: Zemunda

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Misraq » 18 Dec 2023, 10:19

ወንድማችን ሆረስ ብዙ ግዜ ጠቃሚ ሃሳብ ታነሳና የመፍትሄ ሃሳብ ሳትሰነዝር ታልፈዋለህ፥፥ እድሜና እውቀት ጠገብ እንደሆንክ እናውቃለን ስለዚህ እስቲ ኢትዮጵያ ከገባችበት ቅርቃር እንዴት ትውጣና የሁሉም ዜጋ መብት እኩል የሚከበርበትን የነጻነት ፍኖተ ካርታ አሳየን

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Horus » 18 Dec 2023, 16:16

Misraq wrote:
18 Dec 2023, 10:19
ወንድማችን ሆረስ ብዙ ግዜ ጠቃሚ ሃሳብ ታነሳና የመፍትሄ ሃሳብ ሳትሰነዝር ታልፈዋለህ፥፥ እድሜና እውቀት ጠገብ እንደሆንክ እናውቃለን ስለዚህ እስቲ ኢትዮጵያ ከገባችበት ቅርቃር እንዴት ትውጣና የሁሉም ዜጋ መብት እኩል የሚከበርበትን የነጻነት ፍኖተ ካርታ አሳየን
በራስህ ስሜት ተውጠህ ሌሎችን ማዳመጥ አልቻልክም እንጂ ለጥያቄህ ከሞላ ጎደል አበረ ከላይ መልስ እየሰጠህ ነው ።

እኔ እዚህ ፎረማ ላይ ቢያንስ 20 ግዜ የለጠፍኩት ውልፍጥ የማይ አቋምና እምነት አለኝ ።

እሱም የኢትዮጵያ አጀንዳ ይባላል ። ኢትዮጵያ በእውነተኛ ኢትዮጵያዊያን ከተደራጀችና ከተመራች ያላት ብሄራዊ አጀንዳ፣ ያላት ብሄራዊ ፋይዳና ፐርፐዝ በጣም ቀላልና ግልጽ ነው ። ልብ በል ይህ የማንም ጎሳ፣ ቡድን ኃያል ሆነ ደካማ፣ ትንሽ ሆነ ትልቅ ዘውግ ፍላጎትና ህልም አይደለም ፤ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሚሽን ማለት ነው ።

እነሱም 4 ናቸው ፤

ኢትዮጵያ የምትባለው ሕዝብና አገር ብሄራዊ አንድነቷ የጸና፣ ጠንካራና የተረጋጋች (እስቴብል) አገር መሆን አለባት፣ መሆን ነው አላማዋ ። ይህ የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳ ቁጥር አንድ ነው ። ከዚህ አጀንዳ ውጭ የሚያስብ ሁሉ ኢትዮጵያዊ አይደለም፣ እራሱን በፈለገው ስምና ቅጽል ቢጠራ ።

ኢትዮጵያዊ የተባለው ሕዝብ እንደ አንድ የፖለቲካ ማህበረሰብ (Political Community) ፍትህ (እኩልነት)፣ ነጻነት እና ዴሞክራሲ መፈለግ ብቻ አይደለም፤ ያለ ፍትህ፣ ነጻነትና ዴሞክራሲ መኖር አይችልም። ሰላም የሚባል ነገር እስከ አለም ፍጻሜ አያገኝም። ስልጣኔም ሆነ እድገት የሚባል ነገር አይኖሩትም ። ስለዚህ 2ኛው የኢትዮጵያ ፋይዳ፣ የኢትዮጵያ አላማ፣ የኢትዮጵያ ፐርፐዝ ዴሞክራሲ፣ ፍትህና ነጻነትን መወለድና ማሳደግ፣ ማለትም ነጻና ፍትሃዊ ሕዝብ መሆን ነው ። ይህን የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳ ያልገባቸው ወይም የማይቀበሉ ጸረ ኢትዮጵያ ስብስቦች ናቸው የዚህ ሁሉ መከራና ውርደት ምክንያቶች ።

3ኛው የኢትዮጵያ አጀንዳ ኢትዮጵያዊያን የሚባሉት ሕዝብን፣ ዜጋዎችን የበለጸጉ፣ ያደጉ፣ የለሙ፣ የተማሩ እና ጤንነታቸው የተጠበቀ ሕዝብ፣ ዚጋ ማድረግ ነው 3ኛው የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳና ፋይዳ ። ኢትዮጵያ እንደ አንድ አገር፣ እንደ አንድ ሕዝብ፣ እንደ አንድ ማህበር፣ እንደ አንድ ሲስተም አላማ፣ ፋይዳ አላት ። ይህን ፋይዳ ለመተግበር ነው ህያው ሆና ምትቀጥለው ። የኢትዮጵያ አጀንዳን አንድ ሁለት ብለው መቁጠር የማይችሉ መሃይም የጎሳ ጥርቃሞዎች ናቸው የዚህ ሁሉ ሰቆቃ ምክንያቶች ።

በመጨረሻም 4ኛው የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳ የሚፈጥር፣ ችግር የሚፈታ፣ የሚራመድ፣ ከከባቢውና ኢኮሎጂው ጋር የታረቀ፣ አፈሩን። ዉሃውን፣ እንሳሳውን፣ እጸዋቱን፣ አየሩን በሃላፊነት የሚንከባከብ ፣ መንፈሳዊ ፣ በፈጣሪ ኃይል የሚያምን በሞራልና ስነ ምግባር መርሆዎች የተለጎመ ካልቸር መፍጠር፣ መገንባት እና መጠበቅ ነው የመጨረሻው የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳ ። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ካልቸር ምንድን ነው? ምን መሆን አለበት ብለው መጠየቅ የማይችሉ ቀድሞ ነገር እራሳቸው ካልቸር አልባ የሆኑ ከብቶች ናችው በዚህ ታላቅ ሕዝብና ታላቅ አገር ጫንቃ ላይ ተቀምጠው ያለም ማፈሪያ ያደረጉን ።

የኢትዮጵያ መፍትሄ ይህ ብቻ ነው ። ከዚህ ውጭ ያሉት በሙሉ ተፈራራቂ የኢትዮጵያ ጠላቶች ናቸው ። እነዚህ 4 ቀላል ግቦች እንዳይሳኩ ሌት ተቀን የሚባክኑ መሃይሞች፣ እረኞች፣ አረመኔዎችና የውጭ ጥላት አሽከሮች ናቸው ኢትዮጵያን በዚህ መከራ ውስጥ ይዘዋት ያሉት ።

DefendTheTruth
Senior Member
Posts: 11821
Joined: 08 Mar 2014, 16:32

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by DefendTheTruth » 18 Dec 2023, 17:35

Misraq wrote:
18 Dec 2023, 10:19
ወንድማችን ሆረስ ብዙ ግዜ ጠቃሚ ሃሳብ ታነሳና የመፍትሄ ሃሳብ ሳትሰነዝር ታልፈዋለህ፥፥ እድሜና እውቀት ጠገብ እንደሆንክ እናውቃለን ስለዚህ እስቲ ኢትዮጵያ ከገባችበት ቅርቃር እንዴት ትውጣና የሁሉም ዜጋ መብት እኩል የሚከበርበትን የነጻነት ፍኖተ ካርታ አሳየን
ምን አይነት ግፈኛ ነህ፣ አንተስ?

እንድሁ አርጅታሃል አትለዉም በአሽሙር እድሜ ጠገብ ከምትሰደበዉ፣ ሽማግሌ ብለህ?

ሽምግልና እንኳን አልከፋም፣ የሱ ግን ቅሌታም ተሳዳቢ ሽማግሌ በመሆኑ እንጂ።

DefendTheTruth
Senior Member
Posts: 11821
Joined: 08 Mar 2014, 16:32

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by DefendTheTruth » 18 Dec 2023, 17:40

Horus wrote:
18 Dec 2023, 16:16
Misraq wrote:
18 Dec 2023, 10:19
ወንድማችን ሆረስ ብዙ ግዜ ጠቃሚ ሃሳብ ታነሳና የመፍትሄ ሃሳብ ሳትሰነዝር ታልፈዋለህ፥፥ እድሜና እውቀት ጠገብ እንደሆንክ እናውቃለን ስለዚህ እስቲ ኢትዮጵያ ከገባችበት ቅርቃር እንዴት ትውጣና የሁሉም ዜጋ መብት እኩል የሚከበርበትን የነጻነት ፍኖተ ካርታ አሳየን
በራስህ ስሜት ተውጠህ ሌሎችን ማዳመጥ አልቻልክም እንጂ ለጥያቄህ ከሞላ ጎደል አበረ ከላይ መልስ እየሰጠህ ነው ።

እኔ እዚህ ፎረማ ላይ ቢያንስ 20 ግዜ የለጠፍኩት ውልፍጥ የማይ አቋምና እምነት አለኝ ።

እሱም የኢትዮጵያ አጀንዳ ይባላል ። ኢትዮጵያ በእውነተኛ ኢትዮጵያዊያን ከተደራጀችና ከተመራች ያላት ብሄራዊ አጀንዳ፣ ያላት ብሄራዊ ፋይዳና ፐርፐዝ በጣም ቀላልና ግልጽ ነው ። ልብ በል ይህ የማንም ጎሳ፣ ቡድን ኃያል ሆነ ደካማ፣ ትንሽ ሆነ ትልቅ ዘውግ ፍላጎትና ህልም አይደለም ፤ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሚሽን ማለት ነው ።

እነሱም 4 ናቸው ፤

ኢትዮጵያ የምትባለው ሕዝብና አገር ብሄራዊ አንድነቷ የጸና፣ ጠንካራና የተረጋጋች (እስቴብል) አገር መሆን አለባት፣ መሆን ነው አላማዋ ። ይህ የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳ ቁጥር አንድ ነው ። ከዚህ አጀንዳ ውጭ የሚያስብ ሁሉ ኢትዮጵያዊ አይደለም፣ እራሱን በፈለገው ስምና ቅጽል ቢጠራ ።

ኢትዮጵያዊ የተባለው ሕዝብ እንደ አንድ የፖለቲካ ማህበረሰብ (Political Community) ፍትህ (እኩልነት)፣ ነጻነት እና ዴሞክራሲ መፈለግ ብቻ አይደለም፤ ያለ ፍትህ፣ ነጻነትና ዴሞክራሲ መኖር አይችልም። ሰላም የሚባል ነገር እስከ አለም ፍጻሜ አያገኝም። ስልጣኔም ሆነ እድገት የሚባል ነገር አይኖሩትም ። ስለዚህ 2ኛው የኢትዮጵያ ፋይዳ፣ የኢትዮጵያ አላማ፣ የኢትዮጵያ ፐርፐዝ ዴሞክራሲ፣ ፍትህና ነጻነትን መወለድና ማሳደግ፣ ማለትም ነጻና ፍትሃዊ ሕዝብ መሆን ነው ። ይህን የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳ ያልገባቸው ወይም የማይቀበሉ ጸረ ኢትዮጵያ ስብስቦች ናቸው የዚህ ሁሉ መከራና ውርደት ምክንያቶች ።

3ኛው የኢትዮጵያ አጀንዳ ኢትዮጵያዊያን የሚባሉት ሕዝብን፣ ዜጋዎችን የበለጸጉ፣ ያደጉ፣ የለሙ፣ የተማሩ እና ጤንነታቸው የተጠበቀ ሕዝብ፣ ዚጋ ማድረግ ነው 3ኛው የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳና ፋይዳ ። ኢትዮጵያ እንደ አንድ አገር፣ እንደ አንድ ሕዝብ፣ እንደ አንድ ማህበር፣ እንደ አንድ ሲስተም አላማ፣ ፋይዳ አላት ። ይህን ፋይዳ ለመተግበር ነው ህያው ሆና ምትቀጥለው ። የኢትዮጵያ አጀንዳን አንድ ሁለት ብለው መቁጠር የማይችሉ መሃይም የጎሳ ጥርቃሞዎች ናቸው የዚህ ሁሉ ሰቆቃ ምክንያቶች ።

በመጨረሻም 4ኛው የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳ የሚፈጥር፣ ችግር የሚፈታ፣ የሚራመድ፣ ከከባቢውና ኢኮሎጂው ጋር የታረቀ፣ አፈሩን። ዉሃውን፣ እንሳሳውን፣ እጸዋቱን፣ አየሩን በሃላፊነት የሚንከባከብ ፣ መንፈሳዊ ፣ በፈጣሪ ኃይል የሚያምን በሞራልና ስነ ምግባር መርሆዎች የተለጎመ ካልቸር መፍጠር፣ መገንባት እና መጠበቅ ነው የመጨረሻው የኢትዮጵያ ብሄራዊ አጀንዳ ። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ካልቸር ምንድን ነው? ምን መሆን አለበት ብለው መጠየቅ የማይችሉ ቀድሞ ነገር እራሳቸው ካልቸር አልባ የሆኑ ከብቶች ናችው በዚህ ታላቅ ሕዝብና ታላቅ አገር ጫንቃ ላይ ተቀምጠው ያለም ማፈሪያ ያደረጉን ።

የኢትዮጵያ መፍትሄ ይህ ብቻ ነው ። ከዚህ ውጭ ያሉት በሙሉ ተፈራራቂ የኢትዮጵያ ጠላቶች ናቸው ። እነዚህ 4 ቀላል ግቦች እንዳይሳኩ ሌት ተቀን የሚባክኑ መሃይሞች፣ እረኞች፣ አረመኔዎችና የውጭ ጥላት አሽከሮች ናቸው ኢትዮጵያን በዚህ መከራ ውስጥ ይዘዋት ያሉት ።
እንዴ ከከብት እረኛም ጋር እኩል ለመሆን ተዘጋጅቶዋል ማለት ነዉ?

የከብት እረኛዉ ቶሎ ቦታ ይልቅቅልን ስትሉ አልነበረም እንዴ?

Naga Tuma
Member+
Posts: 5944
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Naga Tuma » 19 Dec 2023, 02:27

ምስራቅ፥

ኣንድ ኢትዮጵያዊ ሳይንስ ኣለ።

ሌላ ኢትቶጵያዊ ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ይለምልም ኣለ። በቅንነት ሀሳቡን ጨመረበት።

መፍትሔ የሚጠየቀዉ ችግር ሲኖር ነዉ።

ሳይንስ ማለት እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ይለምልም ማለት ዉስጥ ምን ችግር ኣንብበህ ነዉ መፍትሔ የምትጠይቀዉ?

በሰለጠነ ዓለም የመሪ እናት ዲሞክራሲ ናት። ለዲሞክራሲ አሰራር ደግሞ ሳይንሳዊ ቀመር ወይም ፎርሙላ ኣለ። ለምሳሌ ሱንሱመን ኣስታዉስ። ይህ ስለ ግለሰብ ሳይሆን ስለ አስተሳሰብ ነዉ።

ሆረስ፥

ሳይንስ ብለሃል እና ፎቀቅ ብለህ ወደ ሳይንስ ና።

በተፈጥሮ ጤነኛ ሰዉ በህጻንነት እና ኣዛዉንትነት ዕድሜዎቹ መካካል የመሬትን ስበት ወይም ግራቪቲ በመቋቋም ሙሉ ሰዉነቱን ለኣፍታ ከመሬት ማንሳት ይችላል።

ይህ መዝለልን ይገልጻል።

የመዝለልን ችሎታ ሁሉም ጤነኛ ሰዉ ኣብሮ ይወለዳል።

በተፈጥሮ በአፉ የማይበላ ጤነኛ ሰዉ የለም።

በአፉ የሚበላ በጀርባዉ የማይተነፍስ ጤነኛ ሰዉ ዬለም።

ይህ ማለት በጀርባዉ የማይተነፍስ ጤነኛ ሰዉ ዬለም ማለት ነዉ። ቀላል ሳይንስ ነዉ።

ስለዚህ ምን ያለበት ዝላይ ኣይችልም ያልከዉ የድሮ አባባል ይሆንና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ሲለመልም ምን የሌለበት እና መዝላል የማይችል ጤነኛ ሰዉ ዬለም ይሆናል።

ጆሮ ለባለቤቱ እንግዳ ሆኖብህ ካልሆነ እዚህ ፎረም ላይ በህብረ ትርኢት ስታዝናናን በጀርባህ ስትተነፍስ ያሰማል።

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Horus » 19 Dec 2023, 02:45

Naga Tuma wrote:
19 Dec 2023, 02:27
ምስራቅ፥

ኣንድ ኢትዮጵያዊ ሳይንስ ኣለ።

ሌላ ኢትቶጵያዊ ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ይለምልም ኣለ። በቅንነት ሀሳቡን ጨመረበት።

መፍትሔ የሚጠየቀዉ ችግር ሲኖር ነዉ።

ሳይንስ ማለት እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ይለምልም ማለት ዉስጥ ምን ችግር ኣንብበህ ነዉ መፍትሔ የምትጠይቀዉ?

በሰለጠነ ዓለም የመሪ እናት ዲሞክራሲ ናት። ለዲሞክራሲ አሰራር ደግሞ ሳይንሳዊ ቀመር ወይም ፎርሙላ ኣለ። ለምሳሌ ሱንሱመን ኣስታዉስ። ይህ ስለ ግለሰብ ሳይሆን ስለ አስተሳሰብ ነዉ።

ሆረስ፥

ሳይንስ ብለሃል እና ፎቀቅ ብለህ ወደ ሳይንስ ና።

በተፈጥሮ ጤነኛ ሰዉ በህጻንነት እና ኣዛዉንትነት ዕድሜዎቹ መካካል የመሬትን ስበት ወይም ግራቪቲ በመቋቋም ሙሉ ሰዉነቱን ለኣፍታ ከመሬት ማንሳት ይችላል።

ይህ መዝለልን ይገልጻል።

የመዝለልን ችሎታ ሁሉም ጤነኛ ሰዉ ኣብሮ ይወለዳል።

በተፈጥሮ በአፉ የማይበላ ጤነኛ ሰዉ የለም።

በአፉ የሚበላ በጀርባዉ የማይተነፍስ ጤነኛ ሰዉ ዬለም።

ይህ ማለት በጀርባዉ የማይተነፍስ ጤነኛ ሰዉ ዬለም ማለት ነዉ። ቀላል ሳይንስ ነዉ።

ስለዚህ ምን ያለበት ዝላይ ኣይችልም ያልከዉ የድሮ አባባል ይሆንና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ሲለመልም ምን የሌለበት እና መዝላል የማይችል ጤነኛ ሰዉ ዬለም ይሆናል።

ጆሮ ለባለቤቱ እንግዳ ሆኖብህ ካልሆነ እዚህ ፎረም ላይ በህብረ ትርኢት ስታዝናናን በጀርባህ ስትተነፍስ ያሰማል።
አቶ ናጋቱማ፣
ይህን ንግግርክን በሚገባን ቋንቋ ልትተረጉምልን ትችላለህ? እናመሰኛለን!

Misraq
Senior Member
Posts: 14358
Joined: 27 Sep 2009, 19:43
Location: Zemunda

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Misraq » 19 Dec 2023, 02:45

ወንድሜ ሆረስ

ያቀረብከው ኢትዬጵያዊነት ሃሳብ በprinciple ደረጃ ያስማማል። ነገር ግን ሃሳብህን የትግሬና የኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ሸጠሃል? ከሸጥከውስ ተቀበሉት? እነዚህን ሁለት በጣም የተደራጁና ብዙ ሕዝባቸውን ፅንፍ አስይዘው ያሰለፉ ሃይሎች የማይናቅ ሃይል ገንብተዋል። ሕብረ ብሄራዊ እንቅስቃሴን በክልላቸውም በአዲስ አበባም ሽባ ያደረጉ ሃይሎች እንዴት ወደምትለው ሃሳብ ማምጣት ይቻላል?

እነዚህን ሃይሎች በሃሳብ እምቢ ካሉ በሃይል ወደ ሕብረ ብሄራዊ ፓለቲካ ማምጣት አዋጭ ነው ትላለህ? ካልክስ ተዋጊ ሃይል ከየት ይምጣ ትላለህ? ማንስ ይምራው?

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Horus » 19 Dec 2023, 03:05

Misraq wrote:
19 Dec 2023, 02:45
ወንድሜ ሆረስ

ያቀረብከው ኢትዬጵያዊነት ሃሳብ በprinciple ደረጃ ያስማማል። ነገር ግን ሃሳብህን የትግሬና የኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ሸጠሃል? ከሸጥከውስ ተቀበሉት? እነዚህን ሁለት በጣም የተደራጁና ብዙ ሕዝባቸውን ፅንፍ አስይዘው ያሰለፉ ሃይሎች የማይናቅ ሃይል ገንብተዋል። ሕብረ ብሄራዊ እንቅስቃሴን በክልላቸውም በአዲስ አበባም ሽባ ያደረጉ ሃይሎች እንዴት ወደምትለው ሃሳብ ማምጣት ይቻላል?

እነዚህን ሃይሎች በሃሳብ እምቢ ካሉ በሃይል ወደ ሕብረ ብሄራዊ ፓለቲካ ማምጣት አዋጭ ነው ትላለህ? ካልክስ ተዋጊ ሃይል ከየት ይምጣ ትላለህ? ማንስ ይምራው?
ወንድሜ ምስራቅ፣
ባንጎልህ ውስጥ ያለውን ሃሳብ ትተህ በአይህ የምታየውን ሪያሊቲ ብታምን እንዲህ አትልም ። ትግሬኮ ዛሬ ይህን እያወራን ባላበት ግዜ በረሃብ እየሞተ ነው ። መደራጀት ምናምኑን እርሳው፣ ትግሬ 27 አመት መላ ኢትዮጵያን ይገዛ ነበር ። 4ቱ በጠቀስኩቸው ሃቆች ኃያልነት ከማማው ወርዶ ወደ ረሃቡ ተመልሷል ። ይህ የኢትዮጵያ ሳይንስ ኦሮሙማንም ወደ ትግሬ እጣ ፈንታ ያመጣዋል ። የኢትዮጵያ አጀንዳ የሁሉም ጎሳ መድሃኒት ነው ። ይህ ኢትዮጵያዊ ለመሆን ለምኑኝ የሚለው የጂሎች ዘፈን እርሳው፣ የተበላ እቁም ነው ። ሁሊሽም ለራስሽ ስትል የኢትዮጵያ አጀንዳን ተቀበል ተቀላቀል ! የአረብ ጄት በመዋስ የኦሮሙማ ኢምፓየር አታቆምም! ኢትትዮጵያ ቀኑ ሲደርስ ይህን ያረብ አቃጣሪ ሁሉ ነቅላ ታስወግዳለች!! የኔ ወንድም የፖለቲካ መጀመሪያ የኢትዮጵያን ናሽናል ካራክተር ማወቅ ነው! ይህ ነው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሃ ሁ !

ብሄራዊ አንድነት ክህሎት እንጂ ዝም ብሎ የተሰጠን የንስሳ ባህሪ አይደለም ፣ በጥረትና ልምምድ የምናገኘው ክህሎት ነው !

Right
Member
Posts: 3787
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Right » 19 Dec 2023, 11:03

ከዛሬ እስከ አለም ፍጻሜ አንድ ጎሳ ያሻውን ያክል ቢገነታ የኢትዮጵያን እድል አይወስንም፣ አይቆጣጠርም
ያሻቸውን ያክል ጎሳዎች ቢደመሩ የኢትዮጵያን እድል አይወስኑም
90% of the Ethiopian population knows that and instead of wasting time in this topic Ethiopians should work on the make up and structure of a post PP/EPDRF an all inclusive transitional government practically. That is the key to stop the cycle of conflict.

Fano initiated a resistance under the banner of the Ethiopian flag. And the rest should help it finish the resistance and work on the 2nd phase of the challenge.

tribal elites like Yonas Biru are more worried about a perceived Amhara domination.

Obviously, Ethiopians like the rest of Africans can’t govern themselves. A persistent food insecurity and war are a result of incompetence.

Folks, this tribal nonsense will stop if we put our mind where it should be, changing the Ethiopian constitution based on individual right.

Selam/
Senior Member
Posts: 14362
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Selam/ » 19 Dec 2023, 13:02

- ትክክል ነው ፣ የተረኛነት አስተዳደር ከስሩ ተነቅሎ መወገድ አለበት። ለዚህም መንገዱን ከወዲሁ ለመጥረግ ፣ የተቃውሞ ትግሉ ከብዙ ብሄረሰቦች ጋር ውስጣዊም ውጫዊም የሆነ እውነተኛ ቅንጅት ማድረግን ይፈልጋል።

- የአሸባሪው የወያኔ ህገ-መንግስት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መቀየር አለበት፣ የጎሳ ፖለቲካ አደረጃጀትና ሀገር አከላለል መለወጥ አለበት።

- የማይቀረው የቅርብ ለውጥ ምንድነው ብትለኝ፣ የጎጠኛው የኦነግ-ሸኔ መንግስት ይሰበራል።
Horus wrote:
17 Dec 2023, 02:11
ትግሬ + 0 = ትግሬ አልቻለም
ኦሮሞ + 0 = ኦሮሞ አልቻለም
አማራ + 0 = አማራ አልቻለም
ኦሮሞ + አማራ = ኦሮማራ አልቻለም
ኦሮሞ + ትግሬ = ትግኦሮ አይችልም
አማራ + ትግሬ =አማትግ አይችልም
ኦሮሞ + አማራ + ትግሬ =ኦሮማራትግ አይችልም
ከዛሬ እስከ አለም ፍጻሜ አንድ ጎሳ ያሻውን ያክል ቢገነታ የኢትዮጵያን እድል አይወስንም፣ አይቆጣጠርም
ያሻቸውን ያክል ጎሳዎች ቢደመሩ የኢትዮጵያን እድል አይወስኑም
የማንኛውም የጎሳ በላይነት ሂሳብ ተቃራኒ አፍራሽ የጎሳ ቀመር ይሰራለታል
ይህ ተረት አይደለም! ይህ ምኞት አይደለም
ሳይንስ ነው !

ሆረስ ነኝ


Misraq
Senior Member
Posts: 14358
Joined: 27 Sep 2009, 19:43
Location: Zemunda

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Misraq » 19 Dec 2023, 16:52

Horus wrote:
19 Dec 2023, 03:05
Misraq wrote:
19 Dec 2023, 02:45
ወንድሜ ሆረስ

ያቀረብከው ኢትዬጵያዊነት ሃሳብ በprinciple ደረጃ ያስማማል። ነገር ግን ሃሳብህን የትግሬና የኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ሸጠሃል? ከሸጥከውስ ተቀበሉት? እነዚህን ሁለት በጣም የተደራጁና ብዙ ሕዝባቸውን ፅንፍ አስይዘው ያሰለፉ ሃይሎች የማይናቅ ሃይል ገንብተዋል። ሕብረ ብሄራዊ እንቅስቃሴን በክልላቸውም በአዲስ አበባም ሽባ ያደረጉ ሃይሎች እንዴት ወደምትለው ሃሳብ ማምጣት ይቻላል?

እነዚህን ሃይሎች በሃሳብ እምቢ ካሉ በሃይል ወደ ሕብረ ብሄራዊ ፓለቲካ ማምጣት አዋጭ ነው ትላለህ? ካልክስ ተዋጊ ሃይል ከየት ይምጣ ትላለህ? ማንስ ይምራው?
ወንድሜ ምስራቅ፣
ባንጎልህ ውስጥ ያለውን ሃሳብ ትተህ በአይህ የምታየውን ሪያሊቲ ብታምን እንዲህ አትልም ። ትግሬኮ ዛሬ ይህን እያወራን ባላበት ግዜ በረሃብ እየሞተ ነው ። መደራጀት ምናምኑን እርሳው፣ ትግሬ 27 አመት መላ ኢትዮጵያን ይገዛ ነበር ። 4ቱ በጠቀስኩቸው ሃቆች ኃያልነት ከማማው ወርዶ ወደ ረሃቡ ተመልሷል ። ይህ የኢትዮጵያ ሳይንስ ኦሮሙማንም ወደ ትግሬ እጣ ፈንታ ያመጣዋል ። የኢትዮጵያ አጀንዳ የሁሉም ጎሳ መድሃኒት ነው ። ይህ ኢትዮጵያዊ ለመሆን ለምኑኝ የሚለው የጂሎች ዘፈን እርሳው፣ የተበላ እቁም ነው ። ሁሊሽም ለራስሽ ስትል የኢትዮጵያ አጀንዳን ተቀበል ተቀላቀል ! የአረብ ጄት በመዋስ የኦሮሙማ ኢምፓየር አታቆምም! ኢትትዮጵያ ቀኑ ሲደርስ ይህን ያረብ አቃጣሪ ሁሉ ነቅላ ታስወግዳለች!! የኔ ወንድም የፖለቲካ መጀመሪያ የኢትዮጵያን ናሽናል ካራክተር ማወቅ ነው! ይህ ነው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሃ ሁ !

ብሄራዊ አንድነት ክህሎት እንጂ ዝም ብሎ የተሰጠን የንስሳ ባህሪ አይደለም ፣ በጥረትና ልምምድ የምናገኘው ክህሎት ነው !
ወንድሜ ሆሩስ

ለጥያቄዮ መልስ አልሰጠሀኝም:: እስቲ ድጋሚ አንብበውና ለጥያቄዮ መልስ ስጥ

Naga Tuma
Member+
Posts: 5944
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Naga Tuma » 21 Dec 2023, 20:17

ምስራቅ እና ሆረስ፥

ወደዚህ ርዕስ ኣሁን መመለሴ ነዉ።

ምስራቅ፥

ህብርብሔርን መግለጽ ወይም ድፋይን ማድረግ ትችላለህ?

ሆረስ፥

ሳይስንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ይለምልም ትርጉም ያስፈልጋቸዋል ወይ ብዬ ልሞልጭህ ተነሳሁ እና ይቅር ኣልኩኝ።

ምናልባት ህብረትርኢት ምን ማለት እንደሆነ ካልገባህ ተወዳጅ የሆነ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የሙዚቃ ፕሮግራም ነበረ። ከኪሮስ አለማየሁ እስከ አብተዉ ከበደ፣ ከጎንደር እስክስታ እስከ ጋሞ ጎፋ የወገብ ዉዝዋዜ፣ ከጉራጌ ድለቃ እስከ ሰላሌ ረገዳ።

ጉራግኛ ድለቃ ይሁን ዉዝዋዜ ይባል ተወዳጅ ነዉ። እዚህ ፎረም ላይ የምትለጥፋቸዉ ወደ ጉራግኛ ያደሉ መሆናቸዉ ለዛ ይሁን ለሌላ ኣላዉቅም።

ተተረጎመልህ?

ሁለታችሁንም ይህንን ፎረም ማንበብ ከጀመርኩኝ ግዜ ጀምሮ ግዜ ሳገኝ ኣነባለሁ። ሁለታች ሁም ተመሳሳይ ችግር ኣላችሁ። የማታዉቁትን እንደማታዉቁ ኣለማወቃችሁ። ሳይንሳዊ አስተሳሰብ መንገዱን ይክፈትላችሁ።

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Horus » 21 Dec 2023, 21:36

አቶ ናጋ ቱማ፣
እኔ ላንተ ያለኝ ምክር በተቻለህ መጠን ስለ አንድ ነገር ሶስት ግዜ አስበህ አንዴ ጻፈው፤ የምትለው ነገር ዋጋ እንዲኖረው ማለት ነው ። ይህን ለ60 አመት ተወቅጦ ተወቅጦ ዉሃ የሆነውን የብሄር ጥያቄ ዲሪቶ ወዲያ ብለህ አንጎልክን ነጻ አድርገው ። ህብረ ብሄር የሚለው ቃል ያላዋቂዎች ጭርፍን ድግግሞሽ ነው። ህብር ማለት ማህበር ማለት ነው ፤ ብሄር ማለት ማህበር ማለት ነው ። ሶስቴ ብታስብ ይህን ስሀተት አትደግምም ነበር። የማህበር ማህበር ማለት አላዋቂነት ነው ። የብሄራዊ ኢትዮጵያጵያን ማህበርተኞች 126 ሚሊዮኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ናቸው ። ከዚያ ውጭ ያለውን ሸኔና ሺመልስ ጋ ሄደህ አስተርጉም ።

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም

Post by Horus » 22 Dec 2023, 14:47

ኢትዮጵያን ማሻሻል እንጂ ማፍረስ አይቻልም ። ይህ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ማክሲም ነው ። ይህን አይነኬ እውነታ ለ50 አመት ብንነግራቸውም የጎሳ ፖለቲካ ጂሎች አሁን ህይወት ግዜና ጉልበታቸውን እኔ የፈለኩትን ካላግኘሁ ኢትዮጵያ ትፈርሳለ እያሉ ቡፋ ሲንፉ 50 አመት ደፈነ ። ኦሮሙማ አዲሷ ልገንጠል ባይ ቡፋ ስትነፋ አሁን መላ ኢትዮጵያ ግምባር እየፈጠረባት ነው ። በቃ! ይህ ነው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሳይንስ! ይህ ሁሉ የጂሎች ልፋት ዲሞክራሲና ፍትህ ለማምጣት ቢሆን ዛሬ የት በደረሱ???

የኦሮሙማ ጂሎች ቤተ መንግስትና ድሮን ለመግዛት ሲባክኑ ያባይ ግድብ ግምባታ ቆመ፣ አዲሳባ ደሞዝ
መክፈል አቆመ፣ ወታደር የቅማል ካልሲ በልቶት አለቀ ። ማፈሪያ የብሄር ጥያቂ!




Post Reply