Please wait, video is loading...
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: This BBC news about the military participating in human trafficking
በመከላከያ ሠራዊት ተሽከርካሪ ሲጓዙ የነበሩ 53 ኤርትራውያን ስደተኞች በደቡብ ኢትዮጵያ ተያዙ

ስደተኞቹ ሲጓዙበት ነበረ የተባለው የአገር መከላከያ ተሸከርካሪ
በመከላከያ ሠራዊት ተሽከርካሪ ተጭነው ወደ ኬንያ ሲጓዙ የነበሩ 53 ሕገ-ወጥ ኤርትራውያን ስደተኞችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኧሌ ዞን አስታወቀ።
ሕገ-ወጥ ስደተኞቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከትላንት በስቲያ እሁድ ኅዳር 16/2016 ዓ.ም. ምሽት እንደሆነ የዞኑ ሰላም እና የፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አምሳሉ አንጋቶም ለቢቢሲ ተናግረዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ በደላሎች አማካኝነት ተሰባስበው ጉዞ የጀመሩት ኤርትራውያኑ አዲስ አበባን ጨምሮ ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች መነሻቸውን ያደረጉ ናቸው።
ከተጓዦቹ መካከል ሴቶችም ያሉበት ሲሆን ስድስት ሕጻናትም መኖራቸውን የገለጹት አቶ አምሳሉ፤ ከእነዚህም ውስጥ በወራት የሚቆጠር ዕድሜ ያላቸው እና ጡት የሚጠቡ ሕጻናት ጭምር እንደሚገኙ አስረድተዋል።
ስደተኞቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኧሌ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም በና ጸማይ ወረዳን በሚያዋስ አካባቢ ላይ ሲደርሱ መሆኑን አንድ የአካባቢው ምንጭ ለቢቢሲ ገልጸዋል። በወቅቱ ፓስፖርትን ጨምሮ ሌሎች ሕጋዊ ሰነዶችን እንዲያሳዩ የተጠየቁት ስደተኞቹ ይህንን ማድረግ አለመቻላቸውን እኚሁ ምንጭ ተናግረዋል።
የሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ አምሳሉ በበኩላቸው ስደተኞቹ የተያዙት በአካባቢው የነበሩ የፖሊስ አባላት በጥርጣሬ መኪናውን ካስቆሙ በኋላ መሆኑን አስረድተዋል።
ኤርትራውያኑ የተጫኑት በኢትዯጵያ መከላከያ ሠራዊት “ኦራል” ተሽከርካሪ እንደነበር የገለጹት አቶ አምሳሉ፤ “እነዚህን ያመጣው ደላላ ነው። ደላላው እስከ መከላከያ ሠራዊት ድረስ ገብቶ ጥርጣሬ እንዳይኖር በዚያ መኪና እንዲጫኑ ተደርጓል” ሲሉ ስደተኞቹ በዚህ መኪና እንዲጓዙ ምክንያት ሆኗል ያሉትን ጉዳይ ጠቅሰዋል።

ስደተኞቹ ሲጓዙበት ነበረ የተባለው የአገር መከላከያ ተሸከርካሪ
በመከላከያ ሠራዊት ተሽከርካሪ ተጭነው ወደ ኬንያ ሲጓዙ የነበሩ 53 ሕገ-ወጥ ኤርትራውያን ስደተኞችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኧሌ ዞን አስታወቀ።
ሕገ-ወጥ ስደተኞቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከትላንት በስቲያ እሁድ ኅዳር 16/2016 ዓ.ም. ምሽት እንደሆነ የዞኑ ሰላም እና የፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አምሳሉ አንጋቶም ለቢቢሲ ተናግረዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ በደላሎች አማካኝነት ተሰባስበው ጉዞ የጀመሩት ኤርትራውያኑ አዲስ አበባን ጨምሮ ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች መነሻቸውን ያደረጉ ናቸው።
ከተጓዦቹ መካከል ሴቶችም ያሉበት ሲሆን ስድስት ሕጻናትም መኖራቸውን የገለጹት አቶ አምሳሉ፤ ከእነዚህም ውስጥ በወራት የሚቆጠር ዕድሜ ያላቸው እና ጡት የሚጠቡ ሕጻናት ጭምር እንደሚገኙ አስረድተዋል።
ስደተኞቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኧሌ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም በና ጸማይ ወረዳን በሚያዋስ አካባቢ ላይ ሲደርሱ መሆኑን አንድ የአካባቢው ምንጭ ለቢቢሲ ገልጸዋል። በወቅቱ ፓስፖርትን ጨምሮ ሌሎች ሕጋዊ ሰነዶችን እንዲያሳዩ የተጠየቁት ስደተኞቹ ይህንን ማድረግ አለመቻላቸውን እኚሁ ምንጭ ተናግረዋል።
የሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ አምሳሉ በበኩላቸው ስደተኞቹ የተያዙት በአካባቢው የነበሩ የፖሊስ አባላት በጥርጣሬ መኪናውን ካስቆሙ በኋላ መሆኑን አስረድተዋል።
ኤርትራውያኑ የተጫኑት በኢትዯጵያ መከላከያ ሠራዊት “ኦራል” ተሽከርካሪ እንደነበር የገለጹት አቶ አምሳሉ፤ “እነዚህን ያመጣው ደላላ ነው። ደላላው እስከ መከላከያ ሠራዊት ድረስ ገብቶ ጥርጣሬ እንዳይኖር በዚያ መኪና እንዲጫኑ ተደርጓል” ሲሉ ስደተኞቹ በዚህ መኪና እንዲጓዙ ምክንያት ሆኗል ያሉትን ጉዳይ ጠቅሰዋል።
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44