Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 42663
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

የስነ መንግስት ሕገ ፍትህ እና ፍኖተ ርትዕ!

Post by Horus » 18 Oct 2023, 01:24

እያንዳንዱ ግለሰብ ከሌላው ግለሰብ እኩል ፍጡር ስለሆነ እያንዳንዱ ግለሰብ እኩል መብት፣ ነጻነትና ሃይል አለው ። ይህን ፍጹም መሰረታዊ የስነ ፖለቲካና ስነ መንግስት ሕግ የማይቀበል የሕዝብ መሪ የአገር አስተዳዳሪ የመሆን ምንም አይነት ብቃት የለውም ። ከማንኛውም ያገርና ሕዝብ አስተዳደር ሃላፊነት መወገድ አለበት ።

የአንድ አገርም ሆነ ማንኛውም ማህበራዊ ድርጅት የግለሰቦች ፖለቲካዊና ሕጋዊ እኩልነት የአንድ ስነ መንግስትና ስነ ስርዓር የመጨረሻው የማይጣስ የፍትህ ዶግማ ነው ። በፍትህ ዶግማ ላይ ያልተመሰረተ ስነ መንግስት የግፍና የሕገ አራዊት ስርዓት ነው ። ነጻ ሕዝብ ይህን በመሰለ ስነ መንግስት ውስጥ በፍጹም መኖር ወይም ይህን ለሰው ልጆች የማይመጥን አገዛዝ እምቢ ማለት የተፈጥሮ መብትና ግዴታቸው ነው ።

ፍትህ በሌለበት ሁሉ ግፍ አለ ።

ሌላው ከፍትህ ቀጥሎ ያለው የማንኛውም ስነ ፖለቲካና ስነ መንግስት የማይጣስ ዶግማ ፖለቲካዊ ፍኖተ ርትዕ ነው። በዘመናችን መልካም አስተዳደር (good governance) የተባለው ጽንስ በፖለቲካ ደላሎችና ዲክታተሮች የረከሰ ቃል ቢሆንም በትክክለኛ ኦሪታዊ (ኦሪጂናል) ትርጉሙ የስነ መንግስት ፍኖተ ር ት ዕ ማለት ነው ። ርትዕ እውነት፣ እውነተኛ ማለት ሲሆን ሌላ ትርጉሙ ጥሩ፣ መልካም፣ ያልቆሸሸ፣ በውሸት፣ በሙስና፣ በግፍና ብልግና ያላደፈ ንጹህ ማለት ነው ።

ስለሆነም የስነ መንግስት፣ የስርዓተ አስተዳደር የእውነት መንገድ ምን እንደ ሆነ የማያውቅና ይህን የሚጥስ የሚገድፍ የስነ መንግስት ፍኖተ ርትዕ የማይከተል የሰዎች መሪ ሊሆን አይችልም ። በታሪክ አጋጣሚና አደጋ የመንግስት ስልጣን ይዞ ከሆነም አንድም በሰላም ካልሆነም በጉልበት ከስልጣኑ መወገድ አለበት ። አንድ የነጻ ሕዝብ ሌላ የተፈጥሮ ምብትና ግዴታ ይህን የመሰለ ውሸተኛና ባለጌ የመሪነት አስመሳዮችን ማስወገድ ነው ።

ርትዕ በሌለበት ሁሉ ሌብነት አለ።

ከፍትህና ርትዕ በተጨማሪ ያሉት ዝባዝንኬዎች ሁሉ ዝም ብሎ የስርዓቱ አሸክታቦች ናቸው ።

ሆረስ ዐይነ ብርሃን
Last edited by Horus on 18 Oct 2023, 01:43, edited 1 time in total.

TesfaNews
Member+
Posts: 8149
Joined: 14 Feb 2020, 22:23
Location: Mesob Agezi

Re: የስነ መንግስት ሕገ ፍትህ እና ፍኖተ ርትዕ!

Post by TesfaNews » 18 Oct 2023, 01:40


Horus
Senior Member+
Posts: 42663
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የስነ መንግስት ሕገ ፍትህ እና ፍኖተ ርትዕ!

Post by Horus » 18 Oct 2023, 01:52

TesfaNews wrote:
18 Oct 2023, 01:40
TesfaNews - thanks.

ይቺትልህ አበባ ደሳለኝ ሌላዋ ሂሩት በቀለ ከብዙ አመታት በፊት በሚሊኒየም አዳራሽ!


TesfaNews
Member+
Posts: 8149
Joined: 14 Feb 2020, 22:23
Location: Mesob Agezi

Re: የስነ መንግስት ሕገ ፍትህ እና ፍኖተ ርትዕ!

Post by TesfaNews » 18 Oct 2023, 04:08

Horus wrote:
18 Oct 2023, 02:15




WEEY GUUD!


Horus
Senior Member+
Posts: 42663
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የስነ መንግስት ሕገ ፍትህ እና ፍኖተ ርትዕ!

Post by Horus » 18 Oct 2023, 13:37

ተስፋኒውስ፣
የአቢይ አህመድ ኦሮሙማ ድራማ ፌክ ነው ። የሚዲያ ሽፋን በመቆጣጠር ጸጥ ብለው አማራን እንደ ትግሬ ለማውደምና እስትራተጂካሊ ለማዳከም ነው እንጂ እንኳን ኤርትራ ፈስ ለመዋጋት የሚችል ጦር የለውም አቶ አቢይ !

ኤርትራዊያን አንድ መሳሳት የሌለባቸው ነገር አለ ፤ አቢይን እንጂ ኢትዮያን እንደ አገር ሕዝብ ከመስደብና ከማስቆጣት መጠንቀቅና አቢይን ለማስወደግ ለሚታገለው ሕዝብ የቻሉትን ድጋፍ ማድረግ ነው ።

ይህ የኦሮሞች አጀንዳ ነው፣ የዚያ አጀንዳ ትራፕ ወጥመድ ውስጥ እንዳትገቡ። ይህ ጫጫታ ሁሉ በቅርቡ ጸጥ ይላል !

Post Reply