Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Naga Tuma
Member+
Posts: 7369
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

የሃገር መቅናት እና የሃገር መሸርሸር

Post by Naga Tuma » 03 Aug 2023, 04:57

ወደ እድሜ ባለጸጋነት የደረስኩ ነኝ ማለት ብችልም ከሁለት ትዉልዶች ግዜ በላይ ኖሬኣለሁ ማለት የምችል ኣይዴለሁም።

በእኔ ትዉልድ ዘመን ኣቡን ጴጥሮስን፣ ዘርዓይ ደረስን እና አብዲሳ አጋን ለያይቶ መጥቀስ ኣይቻልም ነበር። የኢትዮጵያ ድንቅ ጀግኖች እና ሰማዕታት ምሳሌዎች ነበሩ።

ፋኖ ከእኔ ትዉልድ በፊት ይታወቅ ነበር። ፋኖ እና አርበኛ ትልቅ ክብር የነበራቸዉ ስያሜዎች ነበሩ። ፋኖ ከተባለ ከሰሜን እስከ ደቡብ እና ከምዕራብ እስከ ምስራቅ የተከበረ ዝና ይመስለኝ ነበር።

የታሪክ ተማሪ ባልሆንም ስማቸዉ ኣብረዉ የሚነሱ ኢትዮጵያዊያንን ኣስታዉሳለሁ። ራስ አሉላ፣ ራስ አበበ፣ በላይ ዘለቀ፣ ጃገማ ኬሎ፣ ገረሱ ዹኪ ኣብረዉ የሚጠቀሱ ስሞች ነበሩ።

ታድያ በዚህ ትዉልድ ዘመን የበላይ ዘለቀ ሠፈር ልጆች ፋኖ ሲሉ ከሰሜን እስከ ደቡብ እና ከምዕራብ እስከ ምስራቅ ፋኖዎች እነ ማን ነበሩ የማይሉት ለምንድነዉ?