Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Right
Member
Posts: 4811
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Ethiopia is interested to engage in a new negotiation on the Nile Dam

Post by Right » 27 Apr 2023, 10:00

ኢትዮጵያ ወደ ሕዳሴ ግድብ ድርድር ለመመለስ ዝግጁ መሆኗን ገለጸች
ታላቁ ሕዳሴ ግድብ
ከ 1 ሰአት በፊት

ኢትዮጵያ በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ያሉ ጉዳዮችን በተመለከተ ከግብፅ እና ከሱዳን ጋር የሚደረገውን የሦስትዮሽ ድርድርን መልሳ ለመጀመር ዝግጁ መሆኗን ገለጸች።

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር አምባሳደር ምስጋኑ አርጋው የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ከሆኑት ማይክ ሐመር ጋር በተወያዩበት ጊዜ ነው የአገራቸውን ፍላጎት የገለጹት።

የታላቁ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ አምባሳደር ምስጋኑ “ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ስር የሚካሄደውን የሦስትዮሽ ድርድርን መልሳ ለመጀመር ዝግጁ ናት” ማለታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በትዊተር ገጹ ላይ አስፍሯል።

ኢትዮጵያ በመጪዎቹ የክረምት ወራት ለአራተኛ ተከታታይ ዓመት ሊጠናቀቅ የተቃረበውን ግድብ በውሃ ለመሙላት እየተዘጋጀች ሲሆን፣ ግብፅ የውሃ ሙሌቱን እና የግድቡ ቀጣይ የሥራ ሁኔታ ላይ ስምምነት እንዲደረግ ትፈልጋለች።

ከጥቂት ሳምንታት በፊት ግብፅ፣ ኢትዮጵያ ድርድር ተደርጎ ስምምነት ሳይደረስ ግዙፉን ግድብ በውሃ መሙላቷን ለመቀጠል ድርድሩን “ለጊዜ መግዣነት እየተጠቀመችበት ነው” ስትል መክሰሷ ይታወሳል።

ሱዳን በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ ተቃውሞ እንደሌላት አስታወቀች27 ጥር 2023
ከጉባ እስከ ፀጥታው ምክር ቤት የደረሰው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ20 የካቲት 2022
በአፍሪካ ግዙፉ የኃይል ማመንጫ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ጀመረ20 የካቲት 2022
ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ መጀመሯን ይፋ ማድረጓን ተከትሎ ከግብፅ እና ከሱዳን በኩል ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠማት ሲሆን፣ የግድቡ ጉዳይም ከአፍሪካ ኅብረት ባሻገር በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥም መነጋገሪያ ሆኖ ነበር።

ሦስቱ አገራት በግድቡ ዙሪያ በተለያዩ ጊዜያት በአፍሪካ ኅብረት እና በአሜሪካ አደራዳሪነት ንግግር ቢያደርጉም ሁሉንም ከሚያግባባ ስምምነት ላይ ሳይደርሱ ቆይተዋል።

ተጠናቆ ሥራውን ሲጀምር በአፍሪካ ግዙፉ እንደሆነ የሚነገርለት ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ አገሪቱ አምስት ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገንዘብ ከራሷ በማውጣት እያከናወነች ነው።

በአፍሪካ ትልቁ የሚባለውን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን እየገነባች ያለችው ኢትዮጵያ፣ ባለፉት ሦስት ዓመታት ግድቡን በውሃ ስትሞላ ቆይታለች።

ግብፅ እና ሱዳን ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው ግዙፍ ግድብን በውሃ መሙላት ከመጀመሯ በፊት አሳሪ ሕጋዊ ስምምነት ላይ መደረስ አለበት በማለት ሲወተውቱ ቢቆዩም፣ ኢትዮጵያ ሳትቀበለው ለሦስት ዙር ግድቡ ውሃ እንዲይዝ አድርጋለች።

ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ በግድቡ ዙሪያ እየተጀመረ ሲቋረጥ የቆየ ድርድር ሲያደርጉ የነበረ ሲሆን፣ ሱዳን እና ግብፅ የግድቡን የውሃ ሙሌት እና ቀጣይ ሥራን በተመለከተ አስገዳጅ ስምምነት እንዲፈረም ግፊት ሲያደርጉ ቆይተዋል።

ኢትዮጵያ ግን በሁለቱ አገራት በኩል የሚቀርቡ የስምምነት ሐሳቦች አብዛኛው ውሃው ከግዛቷ የሚመነጨውን የአባይ ወንዝን በሚያስፈልጋት ሁኔታ ጥቅም ላይ እንዳታውል የሚገድብ ነው ስትል ሳትቀበለው ቀርታለች።

ግንባታው ከተጀመረ ከአስር ዓመት በላይ የሆነው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ፣ 90 በመቶው መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፣ ከአምስት ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለጎረቤት አገራት ኃይል ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።

Right
Member
Posts: 4811
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Re: Ethiopia is interested to engage in a new negotiation on the Nile Dam

Post by Right » 27 Apr 2023, 11:34

That is why the Americans are behaving the way they are behaving.
Delivering to Egypt.

Handling the current Ethiopian government is like a child play for the US diplomats.
The 2 billion dollars the Abiye government is begging for is a simple leverage that will be used as a candy to manipulate the childish PM.

Remember this $2b even it is released is no where near what the spending crazy government requires.

Educator
Member
Posts: 2370
Joined: 03 Jun 2021, 00:14

Re: Ethiopia is interested to engage in a new negotiation on the Nile Dam

Post by Educator » 27 Apr 2023, 11:39

Where is sudan? I don't think there will be anyone on the table from sudan.

Post Reply