Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

The Fake Ethiopianists have successfully completed their entryism of Ethiopian Social Democratic Party ኢሶዴፓ

Post by sarcasm » 01 Jan 2023, 15:35

በኢትዮጵያ ስም ተደራጅተው በመላው ሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የወልቃይት ጉዳይ እንዴት በህገመንግስቱ ይወሰናል .. ለትግራይ በምን መመዘኛ ይመለሳል ብለው ሲጠይቁ ...

ኦሮሚያ ላይ የሚንቀሳቀሰው ኦፌኮ ደግሞ የሻዕቢያ ሰራዊት በቤንሻንጉል በትግራይ በኦሮሚያ እየተንቀሳቀሰ ነው መንግስት ለምን ዝምታን መረጠ ብለው ከሀገር ህዝብና ደህንነት አንፃር የሚቀመጥ ጥያቄን ጠይቀዋል።

በአንድነት ፣ በኢትዮጵያዊነት ስም የሚንቀሳቀሱ የአንድ ወገን ዘረኛ ፓርቲዎች ናቸው የምንለው በምክንያት ነው። በኢትዮጵያ ስም የተቋቋሙ ከጀርባቸው የአንድ ቡድን ጥቅም አስከባሪ የብሔረሰቦች ፀር የሆኑ ፓርቲዎች ናቸው።
.
.
.

Please wait, video is loading...

Abere
Senior Member
Posts: 15446
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: The Fake Ethiopianists have successfully completed their entryism of Ethiopian Social Democratic Party ኢሶዴፓ

Post by Abere » 01 Jan 2023, 16:22

በመሰረቱ ከትግራይ የተወሰደ ወደ ትግራይ የሚመለስ አንዳች ነገር የለም። የወሰደም የሚመልስም የለም። ለትግራይ የሚመለስለት ነገር ቢኖር፤ ሰላም አጥቶ ይኖረ ለነበረው ህዝብ በሰላም በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል እንደ ዜጋ ተንቀሳቅሶ እና ሰርቶ እንድኖር የሚያስችል የስርዐተ መንግስት ዘይቤ ማገኘት ነው።የከሸፈ የወያኔ አስተሳሰብ ይቀጥላል ብሎ የሚያስብ የከሸፈ ህሌና ያለው ነው። ማንም ከማንም ላይ ነጥቆ እና ቀምቶ በመንግስትነት ስም ሰላም ለማምጣት አይችልም። ችሎታም ይሁን ቅቡልነት የለውም። ይህ እንደማይቻል ለእራሱ ለወያኔ ለ27 አመታት በተለይም የአማራ ህዝብ ያስተማረው ብቻ ሳይሆን ወያኔን ስርዐተ መቃብር ያወረደው መሆኑ ይታወቃል። ስለ ወልቃይት ሁመራ አይደለም ትርጉም አልባው የኢትዮጵያ ፓርላማ ማንም ሃያል ሃይል እና አገር አይችልም። አይደለም ስለ አማራ መሬት ለመወሰን አገር በቀላሉ ማስተዳደር የማይችል ወመኔ አንዳች ስለአማራ መሬት እና ህዝብ ማድረግ አይችልም። ይበልጥ የትግራይን ህዝብ ለከፋ የኦነግ መጠቀሚያ ማድረግ ብቻ ነው። የትግራይ ህዝብ በከንቱ በማይጠቅመው እርባናቢስ በሆነው ወያኔ ህልም ባይዋዥቅ መልካም ነው። ጡረታ የወጡ ያረጡ ወያኔዎች አሁንም ያው የጥንቱ መስሏቸው ከንቱ ምኞት ይለጥፋሉ። ኢትዮጵያ አሁን ስለ ወልቃይት እና ሁመራ ሳይሆን መጨነቅ ያለባት የስርዐት ለውጥ ላይ መሆን አለብት። የኢትዮጵያ ችግር የመሬት ችግር አይደለም። የስርዐት ዕጦት ችግር ነው። ይህ ሲፈታ ችግርይ ተፈታ። የወያኔ እና ኦነግ ውልክፍ ስርዐት ጦርነት እና ዕልቂት በይደር የማስቀመጥ እና በስልጣን ለመቆየት እንጅ የክፍለ ሀገር አውራጃ እና ወረዳ ግጭት አይደለም። አገር የጋራ እንጅ የጎሳ አይደለም። ይህ የትግራይ ችግር መሆን የለበትም። የወያኔ ግን ችግር ነው ይህ ካልሆነ መኖር አይችልም። 1 ሚልዮን ትግሬ አስጨርሶ ለመኖር መፈለግ የቱን ያህል ለትግራይ ህዝብ ያላቸው ንቀት ነው። የአማራ ህዝብ ወያኔን በጡጫ አቅምሶ ሸኝቷል የትግራይ ህዝብ ተራነው።

sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

Re: The Fake Ethiopianists have successfully completed their entryism of Ethiopian Social Democratic Party ኢሶዴፓ

Post by sarcasm » 02 Jan 2023, 08:47

"ኢትዮጵያ በአንድ በኩል የባህር በር ስታጣ በሌላ በኩል ደግሞ ወልቃይትን በመቀማት አገሪቱ ከሌላ አገር ጋር እንዳትገናኝ..."--የኢሶዴፓዋ ዶ/ር ራሄል ለመሳይ መኮንን የነገረችው

ወልቃይት ትግራይ ውስጥ መሆኗ ኢትዮጵያን ከማን እንዳትገናኝ እንዳደረገቻት ዶክተሯ ብቻ ነች የምታውቀው። የጂኦግራፊ ዶክተር እንዳትሆን ብቻ 🙊
ወይስ ኢትዮጵያ የምትላት ክልሏን ነው?


Wiz Michael
በነሱ ኣነጋገር ኢትዮጵያ ማለት ኣማራ ማለቷ ነው

Gmk Med
ከኤርትራ ጋር መገናኘት ከተፈለገ 500 ኪ/ሜ የሚሆን ወሰን በአፋር በኩል አላቸው አይደል? ሴትዮዋ እየጠየቀች ያለው በኢ/ያ ስም ስለ አማራ ክልል ነው።
Please wait, video is loading...

sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

Re: The Fake Ethiopianists have successfully completed their entryism of Ethiopian Social Democratic Party ኢሶዴፓ

Post by sarcasm » 02 Jan 2023, 19:30

ቆይ ኢትዮጵያ ከውጪ አገራት ጋር የምትዋሰነው በወልቃይት በኩል ብቻ ነው እንዴ?

በጎንደር-መተማ በኩልና በቤኒሻንጉል በኩል ከሱዳን ጋ አትዋሰንም?
በጋምቤላ በኩልስ ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚያዋስን ድንበር የላትም?
በሞያሌ በኩልስ ከኬኒያ ጋ አትገናኝም?
በሶማሌ ክልልስ በኩል ከሶማሊያ ሪፐብሊክ ጋር አትዋሰንም?
በአፋር በኩልስ ከጂቡቲ ጋር ድንበር አትጋራም?

ሴትዮዋ የምን ዶክተር ናት ለመሆኑ? የዚህ አገር የድ*ድብና inflationማ መጠናት አለበት!

Please wait, video is loading...

Post Reply