Wazema is reporting:-
የአሜሪካ ሁለቱ ሕግ አውጭ ምክር ቤቶች ያጸደቁትንና አሜሪካ ከሱማሌላንድ ራስ ገዝ ሊኖራት ስለሚገባው ግንኙነት የያዘውን ዝርዝር ሕግ ይፋ አድርገዋል። ሕጉ የአሜሪካ መከላክያና ውጭ ጉዳይ ሚንስቴሮች አሜሪካ ለሱማሌላንድ ልትሰጥ የምትችለውን ሁለንተናዊ ድጋፍ፣ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እና የጸጥታ ትብብር የሚመለከት ዓመታዊ ሪፖርት እንዲሁም ፔንታጎን አሜሪካና ሱማሌላንድ ሊኖራቸው ስለሚገባው የጸጥታ ትብብር እስከ ሰኔ ጥናት አድርጎ ለኮንግሬሱ እንዱያቀርቡ ያዛል። ሕጉን ፕሬዝዳንት ባይደን ከፈረሙበት የአገሪቱ ሕግ ሆኖ ሥራ ላይ ይውላል። ሕጉ አሜሪካ ከሱማሌላንድ የሚኖሯትን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት አሜሪካ ከሱማሊያ ጋር ካላት ግንኙነት ነጥሎ የሚመለከትና ሱማሌላንድ በአፍሪካ ቀንድ ቁልፍ የአሜሪካ የጽጥታ አጋርና የጦር ማዕከል እንድትሆን የሚያደርግ ነው። አሜሪካ በሕጓ ሱማሌላንድን ራሷን ችላ ስትጠቅስ የአሁኑ የመጀመሪያ ነው።