Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

አብን የሰሜኑን ጦርነት በሰላማዊ አማራጭ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚደግፍ አስታወቀ። በሰላም ንግግር ሕገ-መንግሥታዊ መርሆች መጠበቅ እንዳለባቸውም አብን ጠቁሟል። EBC

Post by sarcasm » 01 Nov 2022, 19:55

አብን የሰሜኑን ጦርነት በሰላማዊ አማራጭ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚደግፍ አስታወቀ። በሰላም ንግግር ሕገ-መንግሥታዊ መርሆች መጠበቅ እንዳለባቸውም አብን ጠቁሟል።

አብን የሰሜኑን ጦርነት በሰላማዊ አማራጭ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚደግፍ አስታወቀ
*************************

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ /አብን/ የሰሜኑን ጦርነት በሰላማዊ አማራጭ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚደግፍ አስታወቀ።
ፓርቲው በወቅታዊ ጉዳይ በሰጠው መግለጫ፣ ከአሸባሪው ህወሓት ሥሪት እና ባህሪ አንፃር ቡድኑ ሰላምን አማራጭ እንደማያደርግ ገልጿል።
ቡድኑ ለዓመታት በጭቆና ሥራዓት እና ሕዝብን በጠላትነት ጭምር በመፈረጅ ሲንቀሳቀስ የነበረ መሆኑን የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ መልካሙ ሹምዬ ተናግረዋል።

በ3 ዙር ባደረገው ወረራ በአማራ እና አፋር ክልሎች ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ያስከተለው አሸባሪው ህወሓት፣ ለዳግም 4ኛ ዙር ወረራ ጊዜ መግዣ እና የእፎይታ ጊዜ እየፈለገ እንደሆነም ገልጸዋል።

አንዳንድ ምዕራባውያን ሀገራት እና ተቋማት አሸባሪው ህወሓት እንዲያገግም ፍላጎታቸውን እና ድጋፋቸውን በአደባባይ እያሳዩ መሆኑን በመግለጫው ተነሥቷል።

በደቡብ አፍሪካ እየተደረገ ባለው በሰላም ንግግር ሕገ-መንግሥታዊ መርሆች መጠበቅ እንዳለባቸውም አብን ጠቁሟል።
በአማራ እና አፋር የወደሙ ተቋማትን መልሶ ከመገንባት አንፃር ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባም የአብን ሊቀመንበር ዶ/ር በለጠ ሞላ አንሥተዋል።

በሙሉ ግርማይ
Please wait, video is loading...


Abere
Senior Member
Posts: 15459
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: አብን የሰሜኑን ጦርነት በሰላማዊ አማራጭ ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚደግፍ አስታወቀ። በሰላም ንግግር ሕገ-መንግሥታዊ መርሆች መጠበቅ እንዳለባቸውም አብን ጠቁሟል። EBC

Post by Abere » 02 Nov 2022, 11:16

sarcasm,

የአብንን ማህተም የሰረቀ ሰው ነው ይባላል እንደዚህ አይነት መግለጫ የሚሰጠው። This is the job of a hacker. የአብን ህጋዊ እና ኦፊሴላዊ የአቋም መግለጫ አይደለም። አብን ሙሉ በሙሉ የአማራ ወኪሎች ማለት እነ ጀኔራል ተፈራ ማሞን የተመረጡበትን የአማራ ወኪል እንጅ ሌላ አያውቅም - አልተቀበለምም። ይህ የተለጠፈው በብልጽግና በኩል ነው። You are busy try treating the symptom, not the cause. The TPLF's constitution is a null and void thing for the Amhara people - the demographic majority of the country. It is technically null and void. You must find somewhere to sell this cheap trick.

Post Reply