Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 42851
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

የደቡብ አፍሪካው አቺ ቢቺቺ ፤ ትጥቅ ፍታ v. ተኩስ አቁም

Post by Horus » 29 Oct 2022, 16:58

የ6 ቀኑ "ድርድር" አቺ ቢቺቺ ይባላል! ያም ፋይዳ ቢስ ቺት ቻት ማለት ነው!

አንደኛ፣
በጦር ሜዳ ዉጊያ እያሸነፈ ያለ ተከራካሪ ቀድሞ ተኩስ አያቆምም!

ሁለተኛ፣
የኢትዮጵያ አላማ የትግሬን ጦር ማክሰም እንጂ ትህነግን ከሞት አድኖ የዛሬ አመት ሌላ ጦርነት ለመዋጋት አይደለም ። ይህን የሚፈልግ አሜሪካ ነው !

ሶስተኛ፣
ነገ በደቡብ አፍሪካ ምንም አይወሰንም !

አራተኛ፣
ሌላ ቀን በጦር ሜዳው ካለው የሃይል ሚዛን ጋር ተመጣጣኝ የሆነ አዲስ የዲማንድ ሊስት ወጥቶ ለሌላ አቺ ቢቺቺ ቀጠሮ ይደረጋል ።

አምስተኛ።
እስከዚያ የኢትዮጵያ ጦር የትግሬን ሕዝብ ነጻ ማውጣቱን ይቀጥላል!

በአመጽ የሚካሄደው ፖለቲካ በኢትዮጵያ አሸናፊነት ላይ እያለ ለምንድን ነው ኢትዮጵያ በክርክር በሚካሄደው ፖለቲካ እንደትሸነፍ የሚሰበከው፣ አሜሪካ በሉ ወላ አውሮፓ? ገዋ አደረጉን እንዴ :?: :idea: :idea:


Last edited by Horus on 29 Oct 2022, 17:44, edited 1 time in total.

Sam Ebalalehu
Member
Posts: 3639
Joined: 23 Jun 2018, 21:29

Re: የደቡብ አፍሪካው አቺ ቢቺቺ ፤ ትጥቅ ፍታ v. ተኩስ አቁም

Post by Sam Ebalalehu » 29 Oct 2022, 17:19

የ ኢትዮጵያ መንግሥት በ ተኩስ ማቆሙ ተስማምቶአል እኔ እንደምረዳው። ህወሓት ትጥቅ ይፍታ ENDF አንድ ጥይት አይተኩስም ነው ያለው።
ፋይዳ ለሌለው ነገር የሚጠላሉ ፖለቲከኞችን አንድ ቦታ አጉሮ ማነታረክ ምን ይባላል። አሜሪካኖቹም ለዛ ይመስላል አስቀድመው የትእቢት ጅራፋቸውን ያጮሁት። የUN ተወካያቸው መከራ እንደምናይ ነው የሰበከቸው ስምምነት ካልተደረሰ። ትርጉም የስንዴ እቀባ እናረጋለን ነው።
I have news for her. ሰውየው ለራሳችን በቂ ስንዴ ኖሮን ለውጭ አገራት በመጪው ጥቂት አመታት እንሸጣለን እያለ ነው።

Horus
Senior Member+
Posts: 42851
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የደቡብ አፍሪካው አቺ ቢቺቺ ፤ ትጥቅ ፍታ v. ተኩስ አቁም

Post by Horus » 29 Oct 2022, 17:21

ይህው ከ4 ደቂቃ ጀምራችሁ ስሙ! የኢትዮጵያ ጦር አላማ ምን እንደ ሆነ!!!


Horus
Senior Member+
Posts: 42851
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የደቡብ አፍሪካው አቺ ቢቺቺ ፤ ትጥቅ ፍታ v. ተኩስ አቁም

Post by Horus » 29 Oct 2022, 17:34

Sam Ebalalehu wrote:
29 Oct 2022, 17:19
የ ኢትዮጵያ መንግሥት በ ተኩስ ማቆሙ ተስማምቶአል እኔ እንደምረዳው። ህወሓት ትጥቅ ይፍታ ENDF አንድ ጥይት አይተኩስም ነው ያለው።
ፋይዳ ለሌለው ነገር የሚጠላሉ ፖለቲከኞችን አንድ ቦታ አጉሮ ማነታረክ ምን ይባላል። አሜሪካኖቹም ለዛ ይመስላል አስቀድመው የትእቢት ጅራፋቸውን ያጮሁት። የUN ተወካያቸው መከራ እንደምናይ ነው የሰበከቸው ስምምነት ካልተደረሰ። ትርጉም የስንዴ እቀባ እናረጋለን ነው።
I have news for her. ሰውየው ለራሳችን በቂ ስንዴ ኖሮን ለውጭ አገራት በመጪው ጥቂት አመታት እንሸጣለን እያለ ነው።
በፕሪንሲፕል አው ኢትዮጵያ ተኩስ አቁም መች እምቢ ታውቃለች?!

እኔ ሌላ ቦታ ብዬዋለሁ፤ በዚህ ጉዳይ ያሉት ሁለት ድርድሮች ናቸው! አንዱ በኢትዮጵያ መንግስትና በትግሬ ተገንጣዮች መሃል ያለው ትንሹ ድርድር ነው!

ትልቁ እጅግ ግዙፉ ክርክር በልዑል ኢትዮጵያና በሃያሉ አሜሪካ መካከል ያለው ዋናው፣ እጅግ ዋናው ትግል ነው!

ይህን ዋነኛ ረጅም ያሜሪካ ጥቃት ለመቋቋም ብልጽግና አሁን በያዘው የጎሳና የሙስና ቁመና አይችልም! ይህ መሆን አለበት የሁላችን ትልቅ ፍርሃት!

Horus
Senior Member+
Posts: 42851
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የደቡብ አፍሪካው አቺ ቢቺቺ ፤ ትጥቅ ፍታ v. ተኩስ አቁም

Post by Horus » 30 Oct 2022, 12:24

ሆረስ ዐይነ ብርሃን ካህነ አተን ነኝ! ዛሬ የዋሽንግተን ፖስት ይህን አለ! "The outcome of the talks hinges on whether Prime Minister Abiy Ahmed is prepared to give up the momentum achieved by his troops since fighting resumed in late August." እኔ የዛሬ ሳምንት ያልኩት ያን ነበር! ከድርድሩ በፊት! ኢትዮጵያ ፖለቲካውን በጦር ሜዳ እያሸነፈች እያለች፣ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመሸነፍ አትደራደርም ብዬ ነበር ። በቃ! ሃተታ ቢበዛ ባህያ አይጫንም!


Post Reply