አብይ፥ ኢሳያስን፥ የተከተለው፥ ወያኔን፥ እንዲያዳክምለት፥ብሎም፥ እንዲያጠፋለትና፥ ስልጣን፥ ላይ፥ለረጅም፥ ግዜ፥እንዲቆይ፥ የሚያስችለው፥ የደህነት፥ ተቋምና፥ ሌሎችንም፥ ተጋዳኝ፥ ነገሮች፥ እንዲገነባለት ነበር። ኢሳያስ፥ደግሞ፥ አብይን፥ የተቀበለውና፥ መርያችን፥ ትሆናለህ፥ ብሎ፥ ያጃጃለው፥የኢትዮጵያን፥ ሰብአዊ፥ ቁሳዊ፥ ሃብትና፥ የዲፕሎማስያዊ፥ ተፅእኖ፥ ፈጣሪነት፥ ተጠቅሞ፥ ወያኔን፥ ተበቅሎ፥ በማጥፋት፥ እርሱ፥ የሚያስሸከረክራት፥ምዕራብአውያንን፥ የምትገዳደር፥ የአፍርካ፥ ቀንድን፥ መፍጠርና፥ ከተቻለም፥ አፍሪካን፥ በምዕራብአውያን፥ ላይ፥ ለማሳመፅ፥ ነበር።
ኢሳያስም፥ አብይ፥ የሚፈልገውን፥ ነገር፥ ፊት፥ ለፊቱ፥ እያሳዬ፥ ወደማይወጣው፥አዘቅት፥በመጨመር፥ በሬ፥ ሆይ፥በሬ፥ ሆይ፥ ሳሩን፥ ስታይ፥ ገደሉን፥ አላየህ፥ የሚለውን፥ተረት፥ ተርቶበታል። የፖለቲካ፥ ዘመኑንም፥ በአጭር፥ ቀጭቶበታል።