Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 42909
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » 30 Jul 2022, 20:25
እንደ ሚታወቀው ሲዳማ ከደቡብ ከወጣ በኋላ ወያኔዎች ደቡብ ብለው የጠፈጠፉት ቂጣ ሲፈረካከስ ቆይቷል ። ቀጥሎ የተሰራው ከልስተር ደቡብ ምዕራ ክልል የሚባለው ነበር ። ይሀው ዛሬ ደሞ አንድ የኦሞ ክላስተር ሊሰራ ታስቧል። እነሱም ወላይታ፣ ጋሞ ቡርጂ፣ ኮንሶ፣ ባስኬቶና ሌሎች አብሮ ይከሰትራል። ስሙን ማን እንዳሉት ግልጽ አይደለሁም! ኦሞ ሊባል ይቻላል። እዚህ ክለስተር ውስጥ ጋሞ፣ ወላይታ፣ ቡርጂ ክልልነት ሲጠይቁ ነበር።
ሌላው ደሞ ሃዲያ፣ ከምባታ ጥምባሮ፣ ሃላባ ቁሊቶ እና የምን ያካተተ ክለስተር ነው ። የዚያም ስም ማን እንዳሉ አላቅም ግቤ ክልል ሊሆን ይችላል ወይም ደቡብ ሸዋ ሊሉት ይችላሉ ።
በዚህ ዜና ላይ ስለ ጉራጌና ስልጤ የተነሳ ነገር አልሰማንም። ስልጤ ምን እንደ ሚያስብ ባላውቅም ጉራጌ ማንኛውም አይነት ከለስተር ውስጥ መጨፍለቅ ወይም ተከስትሮ መጥፋት አንደ ማይቀበል መላ ጉራጌ ከዳር እስከ ዳር በነቂስ ቅዋሜና ቁጣውን አሳውቋል ። ሌላ ማንኛውም አይነት ስብስብ፣ ምክር ቤት፣ ፓርቲ ወይም ሃይል ጉራጌን በጉልበት ክለሰተር ሊያደርግ እንደ ማይገባውና እንደ ማይችል ህዝባችን በማያሻማ መንገድ አሳውቋል !
Last edited by
Horus on 30 Jul 2022, 20:41, edited 1 time in total.
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 42909
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » 30 Jul 2022, 20:36
ጉራጌ ክልል ነው! መብቱን አክብሩለት! ኬር ለኢትዮጵያ! ሰብኛ ማለቅ ዬሁን !