Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Thomas H
Senior Member
Posts: 13072
Joined: 27 Jan 2007, 16:30
Location: Kaliti
Contact:

አይበልናን ዶ ! የዓብይ መንግሥት ከተበተነ ዱቄት ሆኗል ወደ አደራድሩኝ ልመና በገሃድ ጀመረ

Post by Thomas H » 30 Jul 2022, 13:36

መንግስት፤ ህወሓት የሰላም ሂደቱ ላይ መሰናክል እየፈጠረ በመሆኑ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያሳርፍበት ጠየቀ!

ም/ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የአሜሪካን የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመርን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
አቶ ደመቀ ለልዩ መልዕክተኛው መንግሥት ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እየወሰዳቸው ያሉ ርምጃዎች ላይ ገለጻ ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያወጣው መረጃ ያመለክታል። በዚህም አቶ ደመቀ፤ በአፍሪካ ህብረት መሪነት በቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ አማካኝነት ለተጀመረው የሰላም ጥረት መንግሥት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
መንግሥት ለሰላም ድርድሩ ያለውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ተደራዳሪ ቡድን አቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንም አቶ ደመቀ መኮንን ገልፀዋል። ም/ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተኩስ አቁም ስምምነቱ፣ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ ተጀራሽነት እና ሰብአዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ተጠናክረው እንደቀጠሉም ለልዩ መልዕክተኛው ገልፀዋል።
መንግሥት ለሰላም ድርድሩ ሙሉ ቁርጠኝነቱን እያሳየ ባለበት ወቅት የህወሓት ቡድን በተቃራኒው እያሳያ ያለው አቋም ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በአፍሪካ ህብረት መሪነት በሚካሄደው እንቅስቃሴ ላይ መሰናክል የሚፈጥር በመሆኑ፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቡድኑ ላይ ጫና ሊያሳርፍ ይገባል ማለታቸውንም ከቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።