ኢትዮጵያ ያለባት ዕዳ ስንት ነው? ዕዳዋን ባትከፍልስ ምን ይከተላል?
BBC
22 ሀምሌ 2022
የኢትዮጵያ ዕዳ ከዓመት ዓመት በፍጥነት እያደገ መምጣት ይዟል።
የዓለም ባንክ መረጃ እንደሚያመለክተው ደርግ ከሥልጣን ሲወርድ የኢትዮጵያ ዕዳ 9 ቢሊዮን ዶላር ነበር።
ነገር ግን በ2006 የፈረንጆቹ ዓመት ይህ ዕዳ ወርዶ 2.2 ቢሊዮን ወርዶ የነበረ ቢሆንም፣ ከዚያ በኋላ ግን የኢትዮጵያ ዕዳ ከዓመት ዓመት በቢሊዮን ዶላሮች ይጨምር ያዘ።
የዓለም ባንክ በፈረንጆቹ 2020 ባወጣው መረጃ የአገሪቱ ዕዳ 30.36 ቢሊዮን ዶላር ነበረ።
እነሆ ከሁለት ዓመታት በኋላ ኢትዮጵያ ከአገር ውስጥና ከውጭ የወሰደችው ብድር 56.6 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ይላል የገንዘብ ሚኒስቴር።
የኢትዮጵያ ዕዳ ከአገሪቱ አጠቃላይ ምርት ግማሽ ያክል መሆኑን ተከትሎ ባሉ ወቅታዊ የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ሁኔታዎች ምክንያት አበዳሪዎች በኢትዮጵያ እና በሌሎች አገራት የብድር አከፋፈሉ ዙሪያ ውይይት ይዘዋል።
ከኢትዮጵያ የውጭ አበዳሪዎች የአንበሳውን ድርሻ የምትይዘው ቻይና እንዲሁም ፈረንሳይ ናቸው ስብሰባውን የሚመሩት።
የኢትዮጵያ አበዳሪዎች ዕዳ ስለማሸጋሸግ ውይይት ማድረግ የጀመሩት ባለፈው ዓመት ነበር። ነገር ግን በሰሜን ኢትዮጵያ የተቀሰቀሰው ግጭት ጉዳዩን አጓተተው።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ)፣ የዓለም ባንክ፣ ሌሎች የገንዘብ ተቋማት ቻይና እና ሌሎች አበዳሪዎች ኢትዮጵያ፣ ቻድ እና ዛምቢያ ላለባቸው ዕዳ አስተያየት እንዲያደርጉ በመወትወት ላይ ናቸው።
የአይኤምኤፍ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ዕዳ ኖሮባቸው ተጨማሪ ፈተና እየገጠማቸው ላሉ አገራት መፍትሔ መበጀት አለበት ሲሉ ለሮይተርስ ዜና ወኪል ተናግረዋል።
ለመሆኑ ዕዳ ማሸጋሸግ ምንድን ነው? ኢትዮጵያ ዕዳዋን መክፈል ባትችል ምን ይፈጠራል?
Continue reading https://www.bbc.com/amharic/articles/cn0gy1yvdpzo
Re: የኢትዮጵያ ዕዳ፤ ደርግ ከሥልጣን ሲወርድ 9 ቢሊዮን ዶላር : በ2006 እ.ኤ.አ ይህ ዕዳ ወርዶ 2.2 ቢሊዮን የነበረ ቢሆንም: ኣሁን 56.6 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል - የገንዘብ ሚኒስ
The national debt almost doubled in 2 years between 2020 and 2022! So much for all the funfair of the stewardship of Ethiopian economy by PM Abiy's government.
Re: የኢትዮጵያ ዕዳ፤ ደርግ ከሥልጣን ሲወርድ 9 ቢሊዮን ዶላር : በ2006 እ.ኤ.አ ይህ ዕዳ ወርዶ 2.2 ቢሊዮን የነበረ ቢሆንም: ኣሁን 56.6 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል - የገንዘብ ሚኒስ
"የእናት መቀነት" የኢትዮጵያ እዳ መብዛት ጣጣ