የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ቃፍታ ሽራሮ ብሔራዊ ፓርክ እየደረሰበት ያለውን ጉዳት በማስመልከት ለጉዳቱ መከሰት ምክንያት የሆኑ ክፍቶችን ለማሟላት ቃል ቢገባም አለመፈጸሙን የፓርኩ ሠራተኞች ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።
ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የፓርኩ ሠራተኛ ተቋሙ ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳው አመራሮች፣ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ባለሥልጣናት እንዲሁም ከማኅበረሰቡ ጋር ሚያዚያ 1/2014 ጉዳት እየደረሰበት ላለው ለቃፍታ ሽራሮ ብሔራዊ ፓርክ አራት መሠረታዊ ነገሮች ለማድረግ ቃል ቢገባም አልፈጸመም ብለዋል።
ይሟላሉ ተብለው ከነበሩት አራት መሠረታዊ ነገሮች አንደኛው መጠኑ ባይገለጽም ለፓርኩ የሚያስፈልገው በጀት እንደሚበጀት ነው። ያም እንዳልተሰጣቸውና ወረዳው አቅም ስለሌለው ይህንኑ በጀት በመጠባበቅ ላይ መሆኑን ነው የተናገሩት።
Continue reading https://addismaleda.com/archives/27562