የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም እና አስተማማኝ የኑሮ ዋስትና የሚረጋገጠው ትህነግ-ወያኔ እና ኦነግ-ብልጽግና ሲወገዱ ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ሌላ አማራጭ የለም።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም እና አስተማማኝ የኑሮ ዋስትና የሚረጋገጠው ትህነግ-ወያኔ እና ኦነግ-ብልጽግና ሲወገዱ ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ሌላ አማራጭ የለም።ይህን ለመረዳት ትምህርትም ዕውቀትም አይጠይቅም። ይህ ማለት አንድን ህጻን እሳት ያቃጥላል ወይስ አያቃጥልም ብሎ የመጠየቅ ያህል ነው። ሳንቲም ተከፋይ ወይም በዘመነኛው ቋንቋ ውታፍ ነቃዮችግን ልክ አንዳች ተአምራዊ የሊቃውንት ምርምር የሚፈልግ አድርገውት ከፎረም ላይ ይለጠፋሉ-ምክንያቱም ቋሚ የገቢ ምንጫቸው ስለሆነ። ግጭቱን እና ትርክቱን ከጅምላ ወይም አከፋፋይ ነጋድያን ትህነግ-ወያኔ እና ኦነግ-ብልጽግና ተቀብለው የግደታ ፎረም ላይ ተቀምጠው ችርቻሮ ሲሸጡ መዋል አለባቸው። አንድ የቀረች! አንድ የቀረች! የሚል የውሸት ማደናገርያ እየዘበዘቡ።