Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Abere
Senior Member
Posts: 15492
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

100 ቢልዮን ብር የበላችው ትግራይ ለምን ከሰውነቷን አልተጠጋም? ስንት ብትበላ ይስማማት ይሆን?

Post by Abere » 27 Feb 2022, 11:42

100 ቢልዮን ብር የበላችው ትግራይ ለምን ከሰውነቷን አልተጠጋም? ስንት ብትበላ ይስማማት ይሆን? ይህ ነገር ለጥቂቶች ዕንቆቅልሽ ሊሆን ይችላል። ለብዙዎች ግን ኢትዮጵያ ለትግራይ ከ100 ቢልዮን ብር በላይ እንዳጠፋች እሙን ነው። እንደት? በመጀመሪያ ለ27 አመታት ይህ የአንበሳው ድርሻ ለትግራይ አሰጣጥ ትህነጋዊ ሰራሽ ልማድ ነበረ። እንኳን ዘንቦብሽ እንዳውም ጤዛ ነሽ ይሉ ዘንድ ጦርነት ሲካሄድ ደግሞ በተለይም እንደ አክሱም ኤርፓርት ወደ ሰንዴ ማሳ እርሻነት ተቀይረው ሲታይ የበጀት ጣርያውን ከፈያደርገዋል - ምክንያታዊ ይሆናል። በሁለተኛ ደረጃ ጦርነት የነበረው በትግራይ ክፍለ ሀገር ብቻ ስለሆነ እና እንደ አሁኑ ሌሎች አፋር እና ወሎ በወቅቱ ሰላም ስለነበሩ የበጀቱ ብቸኛ ጠያቂ ትግራይ ስለሆነ - ቸርነቱ ጣርያ አልባ ይሆናል። በሦተኛነት ደረጃ የትግራይ ብልጽግና እና ጊዜያዊ አስተዳዳሪዎች ቁልፍ ወያኔ በመሆናቸው በዘርፍ በዘርፉ ለወያኔ ስራ ማስኪያጃ በቂ ይሆን ዘንድ ሰፊ ድብቅ የበጀት መደብ በማዘጋጀት ግን ተመሳሳይ አስመሳይ የመልሶ ማቋቋም የወጭ ቀዳዳዎች አጋነው ያቀርባሉ። መንግስት ነኝ ባዩ ኦዲፒ ብልጽግና ደግሞ እነዚህን ጊዜያዊ አስተዳዳሪዎች ለማስደሰት ሲባል አይደለም እያለ ከውጭ ተበድሮም ቢሆን ይሰጣል - በወቅቱ በድፍረት ሃላፊነት የወሰዱ ስለሚመስል። ግን አካራሪ ወያኔዎች መሆናቸውን ብዙ ኢትዮጵያዊያን አስገንዝበዋል። ለምሳሌ አብርሃ ደስታ ጽንፈኛ ወያኔ ዳሩ ግን በገጽታ ብቻ(surface level) ተቃዋሚ መሆኑን በርካታዎች አስገንዝበዋል። በአራተኛ ደረጃ ደግሞ ዋናው ዐብይ አህመድ የወያኔ የፍቅር አልጋ ቁራኛ ስለሆነ ለትግራይ ሲባል የአገሪቱን ጥሬት ገልብጦ ቢሰጥ ደስታውን አይችልም። ዐብይ ለትግራይ (ስልጣኑ አይነከባት እንጅ) ቤት ያፈራውን ገልብጦ ሰጥቶ በማግስቱ ልመና ቢሄድ ሃፍረት የለውም። በቅርቡ ለፓርላማ የተናገረው እፍረተቢስነቱ የአፋር እና የወሎ ህዝብ ትግራይን መልሶ ማቋቋም አለብት ያለው በእውነት 100 ቢልዮን ብር ብቻ ነዎይ ሰውየው የሰጠው ብሎ ለማሰብ ያስገድዳል።

ቁም ነገሩ፤ አዎን ትግራይ ከ100 ቢልዮን ብር በላይ በስሶስት ወር ብቻ በልታለች:: ወያኔ ይብላው ወይ ሌላ ያስበሉት ብሩ ተበልቷል። በመሰሩ ድህነቱ ለምን አልጠፋም አይደለም ለምን አልተቀነሰም ይህን ያህል የ10 አመት በጀት ተበልቶ ነው። ለነገሩ ድህነት አይጠፋም ይቀንሳል እንጅ መጽሃፍ ቅዱስ ይላል “ድሆች ዘወትር ከእናንተ ጋር ናቸው”።

Abere
Senior Member
Posts: 15492
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: 100 ቢልዮን ብር የበላችው ትግራይ ለምን ከሰውነቷን አልተጠጋም? ስንት ብትበላ ይስማማት ይሆን?

Post by Abere » 28 Feb 2022, 09:54

አሁን መሆን ያለበት ጥያቄ ከዚህ በፊት ስለተቆረጠመው 100 ቢልዮን ብር ሳይሆን ከዛ ወድህ ስንት ቢልዮን ብር ጠፋ፤ ማነው የሚያጠፋው፤ለምን ለምን ጉዳዮች የሚለው አንገብጋቢ ጥያቄ ነው። በትግራይ አግባብ ያለው የበጀት አመዳደብ የወጭ ስርዐት እና የኦዲት ክትትል ማድረግ አይቻልም - ምክንያቱም ተጠያቂ ሊሆን የሚችል የመንግስት መዋቅር እና ተቋማዊ ባለስልጣን የለም። በጀት ለሽፍታ መመደብ አይቻልም ሽፍታ ሃላፊነትም ተጠያቂነትም የለውም በበጀት አፈጻጸም ላይ። ስለዚህ ትግራይ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ያላት ግንኙነት በወያኔ በኩል ሊፈጸም አይችልም። የአገር እና የህዝብ ሃብት የእያንዳንዱ ግብር ከፋይ ንብረት በሽፍታ እንድ መዘበር ማድረግ አይቻልም። የትግራይ ህዝብ የኑሮ እና የኢኮኖሚ ቀውስ ምክንያት የሆነው ወያኔ ነው። ወያኔን እንደ አዞ ቀልቦ እያወፈሩ ትግራይን ነጻ ማውጣት አይችላም። የኢትዮጵያ ህዝብም በባርነት ላይ ለሚገኘው ለትግራይ በጀት የመመደብ ግደታ የለበትም። በውል ከሄደችው በቅሎየ ያለውል የተበላችው ቆሎየ ታናድደኛለች ይላል አማራ ሲተርት። በጀት በውል በህግ እና በተጠያቂነት ላይ እንጅ ለወሮ በላ አይሰጥም - ዶ/ር ሙሉ የሚሉት የትግራይ ወሮ ባላ 100 ቢልዮን ብር አስጠትቶ አፉን ሲከፍት ይገርመኛል። ለምን ወያኔ ጋር አይቀርም ነበር የአዲስ አበባውን የከተማ ወያኔ ከሚቀላቀል? መሪ አለመኖሩን አውቆ ነው።

Post Reply