Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

የአሜሪካ ኤምባሲ በመቀሌ በከፈተው ጊዜያዊ ቢሮ የኮንሱላር አገልገሎት መስጠት ጀመረ (ዋዜማ ራዲዮ)

Post by sarcasm » 22 Feb 2022, 08:46

የአሜሪካ ኤምባሲ በመቀሌ በከፈተው ጊዜያዊ ቢሮ የኮንሱላር አገልገሎት መስጠት ጀመረ


ዋዜማ ራዲዮ- በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በትግራይ ክልል መቀሌ በከፈተው አዲስ ጊዜያዊ የመስክ ቢሮ የኮንሱላር አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ዋዜማ ስምታለች።

ኤምባሲው አዲስ አገልገሎት የጀመረውና የመስክ ቢሮም የከፈተው በክልሉ የሚኖሩ የአሜሪካ ዜግነት ያላቸውን ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና አሜሪካውያንን ከነቤተሰቦቻቸው ለመድረስ ታስቦ መሆኑን የኤምባሲው ምንጮቻችን ለዋዜማ ተናግረዋል።

ኤምባሲው የመስክ ቢሮውን እንዲከፍት ያስገደደው በትግራይና በማዕከላዊ መንግስት መካከል የትራንስፖርትም ሆነ የመገናኛ አውታር በመቋረጡ ከአዲስ አበባ ሆኖ አገልግሎት መስጠት ባለመቻሉ ነው።

ባለፈው ዓመት በትግራይ ጦርነቱ ተፋፍሞ በነበረበት ወቅት የአሜሪካ መንግስት ዜጎቹን ከክልሉ ለማስወጣት ጥያቄ ቢያቀርብም ከሁለቱም ተፋላሚዎ ይሁንታ ባለማግኘቱ በርካታ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሉበት እንዲቆዩ ተገደዋል።

ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ሕይወታቸው ያለፈና የተሰወሩ የአሜሪካ ዜግነት ያላቸውን ግለሰቦች ከመመዝገብ አንስቶ ማንነታቸውን የሚገልፅ ስነድ ለጠፋባቸው ዜጎች ጊዜያዊ የጉዞ ሰነድ በማዘጋጀት ወደ መኖሪያ ሀገራቸው አሜሪካ እንዲመለሱ ለማድረግ እየተሞከረ ነው።

በተለይም ለቅርብ ቤተሰቦቻቸው የጉዞ ሂደት ለማመቻቸት የሚፈልጉ እና አዲስ አበባ ወደሚገኘው ኤምባሲ ቀርቦ ሂደቱን ለማስፈፀም ለተቸገሩ የክልሉ ነዋሪዎችን አገልግሎት ለመስጠት እንደታሰበም ተነግሯል።

አንዳንድ ባለጉዳዮች ጊዜያዊ ሰነድ ካገኙ በኋላ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከነቤተሰቦቻቸው አልያም በተናጠል ከሀገር መውጣት የሚያስችላቸው የተሟላ ሰነድ ያገኛሉ ተብሏል።

እነዚህን ዜጎችና ቤተሰቦቻቸውን በልዩ በረራ ከትግራይ በቀጥታ ወደ ውጪ ሀገር ለመውሰድ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነት መኖሩን የሚያረጋግጥ መረጃ ዋዜማ አላገኘችም። [ዋዜማ ራዲዮ]

http://wazemaradio.com/%e1%8b%a8%e1%8a% ... %e1%8b%ab/


Cigar
Senior Member
Posts: 12407
Joined: 19 Apr 2010, 00:03

Re: የአሜሪካ ኤምባሲ በመቀሌ በከፈተው ጊዜያዊ ቢሮ የኮንሱላር አገልገሎት መስጠት ጀመረ (ዋዜማ ራዲዮ)

Post by Cigar » 22 Feb 2022, 10:07

It is mission impossible to open a consulate in chgray, Ethiopian region with out the approval of the Ethio federal govt and I am certain that the Ethio govt won’t fu”cken allow it.
Agames are happpy playing a little tigray republic game.
You funfunat agames tribes, just grow some balls and secede from Ethiopia and you can have any embassy in your dirty, beggar tigray.
There is no freaking American agames citizen in tigray that the USA can worry about.
If the diaspora American agames want to go to tigray or leave tigray, they need to deal with the Ethiopian foreign offices for entry or exit visas and pass through Bole airport.


AbebeB
Member+
Posts: 7694
Joined: 15 Oct 2016, 10:31

Re: የአሜሪካ ኤምባሲ በመቀሌ በከፈተው ጊዜያዊ ቢሮ የኮንሱላር አገልገሎት መስጠት ጀመረ (ዋዜማ ራዲዮ)

Post by AbebeB » 22 Feb 2022, 18:16

sarcasm wrote:
22 Feb 2022, 08:46
የአሜሪካ ኤምባሲ በመቀሌ በከፈተው ጊዜያዊ ቢሮ የኮንሱላር አገልገሎት መስጠት ጀመረ

ዋዜማ ራዲዮ- በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በትግራይ ክልል መቀሌ በከፈተው አዲስ ጊዜያዊ የመስክ ቢሮ የኮንሱላር አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ዋዜማ ስምታለች።
sarcasm,
I think I will the first fully fledged Ambassador of Oromia in Mekelle. በዚያውም የፈትኃት ሚስቴን አገኛታለሁ፡፡
:roll: :| :roll:

sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

Re: የአሜሪካ ኤምባሲ በመቀሌ በከፈተው ጊዜያዊ ቢሮ የኮንሱላር አገልገሎት መስጠት ጀመረ (ዋዜማ ራዲዮ)

Post by sarcasm » 22 Feb 2022, 20:33

AbebeB wrote:
22 Feb 2022, 18:16
sarcasm wrote:
22 Feb 2022, 08:46
የአሜሪካ ኤምባሲ በመቀሌ በከፈተው ጊዜያዊ ቢሮ የኮንሱላር አገልገሎት መስጠት ጀመረ

ዋዜማ ራዲዮ- በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በትግራይ ክልል መቀሌ በከፈተው አዲስ ጊዜያዊ የመስክ ቢሮ የኮንሱላር አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ዋዜማ ስምታለች።
sarcasm,
I think I will the first fully fledged Ambassador of Oromia in Mekelle. በዚያውም የፈትኃት ሚስቴን አገኛታለሁ፡፡
:roll: :| :roll:
I think we will see a lot of positive change in the near future. The blockade should end very soon and normalcy would return in all types of transportation, banking, communication etc.

Post Reply