Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
DefendTheTruth
Senior Member
Posts: 13257
Joined: 08 Mar 2014, 16:32

Iran officially joined in the NoMore Movement

Post by DefendTheTruth » 13 Dec 2021, 10:45

Please wait, video is loading...
#NoMore!
የኢራን ወታደራዊ አዛዥ #ጀነራል_አሽራፍ _ናስር_አብደል_ቀኒ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳይ በማስመልከት ለ #PressTV በሰጡት መግለጫ፦
"ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አይን እየገለጠችላቸው ነው በአሜሪካ ሴራ መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ ድንጋይ ዘመን ተመልሰዋል። ይሄ ሁሉ ሲሆን ኢራን መንግስትና ህዝብ በብቸኝነት ለሀገራቶቹ መንግስት ሲከላከልና የአሜሪካን ጣልቃ ገብነት ስንቃወም ቆይተናል። ሆኖም እኛን አድማጭ አጥተን እና በአለማቀፉ ማህበረሰብ በሽብርተኝነት እንድንያዝና በፀጥታው ምክር ቤት ተደጋጋሚ ማዕቀብ ሲጣሉብን ከርመናል ፤ ሰሚ ግን አላገኘንም።
የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ተደማጭነትና ከቀድሞ አባቶቻቸው የወረሱት ለቅኝ ገዢዎች አንገዛም ባይነት ታሪካቸው ለዛሬው የአሜሪካ ቅሌት እንዲጋለጥ ጠቅሟታል። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ የራሷን ብቻ ሳይሆን ብዙ የታፈኑ የአለም ሀገራትን እኛን ጨምሮ ድምፃችን እንዲሰማ ምክንያት ሆናለች።
አሁን የቅኝ ገዚ እሳቤ ያልተላቀቀችሁ ሀገረ አሜሪካ ዲፕሎማሲዋ አፈር በልቷል። ቀኗም እየጨለመ ነው። በአለም ላይ ካሉት 171 ሀገራት 100ና ከዚያ በላይ የሆኑት ከኢትዮጵያ ጎን ቆመው አሜሪካንን እያወገዙ ነው።
ኢትዮጵያ የሁላችንንም በደል ገልፃለች ለዚህም እናመሰግናታለን ! ! !
ከጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ ጋርም አብረን ለመዝመት ፈቃደኞች ነን። ከዚህ በተጨማሪም ኢራን ለኢትዮጵያ ህግ ማስከበር ዘመቻ ሁለት (2) ዘመናዊ ድሮኖችን ለመስጠት ቃል ገብታለች ሲሉ ገልፀዋል።
እኛም እናመሰግናለን!