ከሚሴ ገብቶ የነበረው የህወሃት ታጣቂ በወሎ ኦሮሞ ወጣቶች ተመቶ መውጫ ሲያጣ ወደ አጎራባች የሰሜን ሸዋ ወረዳዎች ቢሸሸም፥ በአንጾኪያ ገምዛ ወጣቶች ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ተደምስሷል። ከሚሴ ሙሉ በሙሉ ከህወሃት ጸድታለች!
Re: ልዩ መረጃ!"እንደወጣች ቀረች"
እሮብ ከሰዓት በሁላ ከሚሴ ገብቶ የነበረው የህወሃት ታጣቂ ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል። በወሎ ኦሮሞ ወጣቶች ተመቶ መውጫ ሲያጣ ወደ አጎራባች የሰሜን ሸዋ ወረዳዎች ሸሽቶ የነበረው የህወሃት ታጣቂ በአንጾኪያ ገምዛ ወጣቶች ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ተደምስሷል። ከሚሴ ሙሉ በሙሉ ከህወሃት ጸድታለች። ከከሚሴ ወጥተው የነበሩት የዞኑ አመራሮች የዞኑን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሃሰንን ጨምሮ በአሁኑ ሰዓት በመከላከያ ታጅበው ወደ ከሚሴ እየሄዱ ነው።