ከአሁን በኋላ የማንንም ተኳሽና አስተኳሽ ታቅፈን እየቀለብንና በይሉኝታ ተቀፍድደን በመድፍ የምንደበደብበት አንዳች ምክንያት አይኖርም። ጋሻው መርሻንና እኔን ለመምታት ሶስት መድፍ ተተኩሷል። አንዱ መኪናችንን ስቷል፣ ሌላው የመኝታ ክፍላችንን አፍርሷል። ከተኳሹ አስተኳሹ!
ከ30000 በላይ የትህነግ አስተኳሽ ታቅፎ የሚኖረው የደሴ ከተማ ህዝብ ከውስጥ ባይተኮስበት፣ በውዥንብር ባይፈታ ነበር የሚገርመው። ግን ይሄን ምስኪን ህዝብ የሚያስብለትና የሚያስተዳድረው ማን ነው?
ደሴ ከተማ ለመግባት ከሞከረው ወራሪ ጋር መቀሌ እንደምንገናኝ ስነግራችሁ "የማይሰበር፣ የማይነጥፍ ቃል" መሆኑን በማረጋገጥ ነው።
ከዚህ በኋላ በትግላችን እቀልዳለሁ ወይም አላግጣለሁ የሚል ካለ የብረት ገላ ካለው ብቻ ይሞክረው! እጅግ መራር በሆነ ምዕራፍ እንገናኝ!!!
የአብኑ የሱፍ ኢብራሂም ከደሴ
