
natnaelmekonnen21's profile picture
natnaelmekonnen21
#Ethiopia : የህወሓት የሽብር ቡድን ታጣቂዎች ሰርገው በገቡባቸው አካባቢዎች እየተደመሰሱ መሆኑን የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዩች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ገልጸዋል፡፡
የህወሓት የሽብር ቡድን ታጣቂዎች በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎችን በኃይል ወረዋል ያሉት ዳይሬክተሩ ሰርገው በገቡባቸው ቦታዎች ግድያ፣ ዘረፋ እና አስገድዶ መድፈር እየፈፀሙ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች ሰርገው በገቡባቸው አካባቢዎች እየተደመሰሱ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ከኢቲቪ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ገልፀዋል፡፡
አቶ ግዛቸው የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች ሰርገው ከገቡበት አካባቢዎች ጠራርጎ ለማስወጣትና ለመደምሰስ ሁሉም የፀጥታ ሃይሎች በቂ የሥነ-ልቦና እና አካላዊ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
የህወሓት የሽብር ቡድን "ይህንን ቦታ ያዝን ፣ያንን ቦታ ተቆጣጠርን " እያለ በሚነዛው ፕሮፖጋንዳ ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ ትክክለኛ መረጃን ከመንግስት አካላት ማግኘት እንዳለበት ዋና ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ህብረተሰቡ በተለይ ወጣቱ አካባቢውን በንቃት እና በትጋት በመከታተል እና በመደራጀት ለሰላሙ ዘብ ሊቆም የገባል ብለዋል፡፡