በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ውስጥ የሴዳል ወረዳ ከተማ የሆነችውን ዲዛንን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ያዋለው የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ (ጉሕዴን) መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ገለጸ።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር የሆኑት ምስጋናው እንጂፋታ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት ታጣቂው በክልሉ ውስጥ ካሉ ሦስት ዞኖች በካማሺ ውስጥ የሚገኘውን የሴዳል ወረዳ ከተማን ተቆጣጥሮታል።
በምዕራብ ኢትዮጵያ ቤኒንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ ካማሺ ዞን ውስጥ የሚገኘው ሴዳል የወረዳ በታጣቂዎች ቁጥጥር ሰር መዋሉን ቀድሞ ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ነው።
Please wait, video is loading...