Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 42514
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

ብልጽግና የጎሳ ቡድኖች ጥርቃሞ እንጂ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ፖለቲካ ፓርቲ አይደለም

Post by Horus » 30 Mar 2021, 00:12

ይህ የማህበረ ሰብ ሳይንስ ነው። የትግሬ ብልጽግና ፓርት፣ ያማራ ብልጽግና ፓርት፣ [deleted] ብልጽግና ፓርት፣ የኦሮሞ ብልጽግና ፓርት፣ የሱማሌ ብልጽግና ፓርት፣ የደቡብ ዕራብ ብልጽግና ፓርት፣ ያዲሳባ ብልጽግና ፓርት፣ የሚባሉት የጎሳ ቦድኖች በቅርቡ እርስ በርስ ይዋጋሉ ወይም ይፈርሳሉ ።

ብልጽግና ፓርት አንድ ድርጅት ሆኖ መቀጠላ ካሻው የጎሳ ክልሎችን አፍርሶ የኢትዮጵያ ፓርቲ መሆን ግድ ይለዋል ። አሁን ያለው ብልጽግና ፓርት የዘር ፓርቲ እንጂ የኢትዮጵያ ፓርቲ አይደለም !!

Last edited by Horus on 30 Mar 2021, 01:42, edited 1 time in total.

Horus
Senior Member+
Posts: 42514
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ብልጽግና የጎሳ ቡድኖች ጥርቃሞ እንጂ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ፓርቲ አይደለም

Post by Horus » 30 Mar 2021, 00:33

ብልጽግና አንድ ጎሳ ከሌላ ጎሳ እንዴት እንደ ሚበልጥና ይበልጥ ሃያል ጦር አቁሞ ለማይቀረው የእርስ በርስ ጦርነት መዘጋጂያ የዉሸት ግዜያዊ ቅንጅት እንጂ እውነተኛ የኢትዮጵያ ድርጅት ከቶም ሊሆን አይችልም ። አንድ ሰው በኢትዮጲያወነቱ የምት ሄዶ መናገር፣ ምደራጀት፣ መመረጥ የማይልበት ጭራቅ የሆነ የፖለቲካና የፓርቲ ሲስተም ኢትዮጵያዊ ብሎ የሚጠራው ካለ እሱ ደደብ የፖልቲካ ደንቆሮ ማለት ነው።

TGAA
Member+
Posts: 5747
Joined: 07 Apr 2019, 20:34

Re: ብልጽግና የጎሳ ቡድኖች ጥርቃሞ እንጂ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ፓርቲ አይደለም

Post by TGAA » 30 Mar 2021, 00:36

Prosperity party by design is the most deformed party that ever existed. It has a Ethiopian nationalistic aspirations, democratic wishes , and capitalist drive but it tries to plant all these in weyene kill farm, watering it with hate, covering all telltale signs of Ethnic cleansing .

Masud
Member+
Posts: 8502
Joined: 18 Jun 2013, 09:06

Re: ብልጽግና የጎሳ ቡድኖች ጥርቃሞ እንጂ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ፓርቲ አይደለም

Post by Masud » 30 Mar 2021, 00:37

Yes in the eyes of Fuga Uragies, but it is recognized political party and ruling party. Duqet!

Horus
Senior Member+
Posts: 42514
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ብልጽግና የጎሳ ቡድኖች ጥርቃሞ እንጂ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ፓርቲ አይደለም

Post by Horus » 30 Mar 2021, 00:55

አንድ ዘመናዊ የፖለቲካ ፓርቲ ከዘመናዊ የፖለቲካ ሲስተም ጋር የተሳሰረ ነው። አንድ መንንግስት ማለት ያንድ አገር እስቴት የሚመራውና ፖሊሲ የሚያወጡለት ፓርቲዎች ናቸው። 9 የተለያዩ ጎሳዎች ሁሉም አንዱን ለመቅደም በሰላምም በጦርም የሚዋጉ የዘር ፓርቲዎች የኢትዮጵያ አንድ ሃገራዊ ፖሊሲና ኢትዮጵያዊያን በግለሰብ ዜግነታቸው የሚያከብር፣ የሚያስችል ፓርቲ ከቶን ሊሆን አይችልም። ይህ የዘር ጥርቃሞ ዞሮ ዞሮ የጎሳ ከበርቴው ኪራይና ጉቦ መሰብሰቢያ መሬት መቸብቸቢያ መሳሪያ ነው የሚሆነው !

Horus
Senior Member+
Posts: 42514
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ብልጽግና የጎሳ ቡድኖች ጥርቃሞ እንጂ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ፓርቲ አይደለም

Post by Horus » 30 Mar 2021, 01:40

የብልጽኛ ፓርቲ ትልቅ ድክመትና ያቢይ አህመድም ደካማ ጎን ምን እንደ ሆነ ልንገራችሁ ።
መደመር ያቢይ ሃሳብ እንጂ የብልጽግና ሃሳብ አይደለም ። ብልጽኛ የአንድ ፓርቲ እስትራተጂ (አሰራር ዘዴ) እንጂ ፍልስፍናም፣ ቲኦሪም፣ ር ዕዮተ አለም አይደለም። በደመመር በሚባል የማህበረ ሰብ ሳይንስ የቆመ የንግስት ስርዓት የለም ።

ትልቁ ስህተትና ድክመት መደመር ማለት አቢይ እንጂ ብልጽግና አይደለም ።

መደመር የሚባለው ሃስብ በአቢይ አህመድ አንጎል ወስጥ ህብር፣ ውህደት፣ ቅንብር ሊኖረው ይችላል ። ግን በብልጽግና አባልትና እና በድርጅቱ ውስጥ ያለ ርዕዮተ አለም አይደለም።

ስለዚህ ትልቁ የዚህ ፓርቲ ድክመትና ያቢይም ድክመት አቢይ አህመድ እና ብልጽግና ፓርቲ ለየቅልና አንድ ያልሆኑ ነገሮች ናቸው።

አቢይ የሚፈልገው በግለ ሰብ ዜጋ ላይ የተደራጀ አገራዊ ኢትዮጵያዊ ፓርቲና ፕሬዚዳንታዊ የመንግስት አወቃቀር ነው።

ብልጽግና ግን በውጭ መልኩና በመልክቱ ያቢይ አህመድ ምስል ይመስላል ፤ በውስጡና በተግባሩ እንደ ኩበት የተፍረከረከ የጎሳ ጥርቃሞ ነው ።

ይህ ነው የዚያ ፓርቲ ግዙፍ ድክመት !

Post Reply