ሰበር ዜና፣ የጁንታው ጦር አዛዦችና ሚሊሻዎች ውስጥ 110 የጁንታዉ ሰራዊትና ሚሊሻ ኮረም ላይ ተማርከዋል
ከቆላ ተምቤን ሸሽቶ ለሁለት በመከፈል ከተበታተነው የጁንታው ጦር አዛዦችና ሚሊሻዎች ውስጥ 110 የጁንታዉ ሰራዊትና ሚሊሻ ኮረም ላይ ተማርከዋል:: ከምርከኞቹ መካከል ከመከላከያ የከዱ ኮረኔል ሀዲሽ ሁሉፍ ሻለቃ ባሻ ጉኡሽ ሻንበል ጌታቸዉ ከሰራዊቱ ጋር አብረው ተማርከዋል:: በተያያዘ ዜና የቀድሞ የማእከላዊ እዝ ምክትል አዛዥና የጄኔራል አበባው ታደሰ ምክትል የነበረዉ ብርጋዴን ጀነራል አብረሀ (ድንኩል) ከ8 ኮረኔሎች ጋር መደምሰሱ ተረጋግጧል::