ብልፅግና አንድ ተቋም እሰከሆነ ድረስ የትኛውም አካል ለሚፈፅመው ጥፋት ፓርቲው ኃላፊነት ሊወስድ እና ተጠያቂ ሊሆን ይገባል - ኢዜማ
የኢዜማ ምክትል መሪ አንዷለም አራጌ እንዳሉት የከንቲባ ሹመት ሂደቱ ጉልቻ ቢቀየር ወጥ አያጣፍጥ ነውና ትክክለኛ መፍትሄ መሆን ያለበት ህዝቡ በሚፈልገው መንገድ ከንቲባውን እንዲመርጥ ምርጫ ማካሄድ ብቻ ነው ብለዋል። ሀገራዊ ምርጫም ቢሆን በቀጣይ ጊዜ ስለመካሄዱ የሚያመላክት ፍንጭ የለም የሚሉት ምክትል መሪው በሀገሪቱ ምርጫ የሌለ እስኪመስል ድረስ ለምርጫ የሚደረገው እንቅስቃሴ ሞቷል ብለዋል።
Watch VIDEO Here - https://mereja.com/video2/watch.php?vid=a5e62fb4a
