Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sesame
Member+
Posts: 8429
Joined: 28 Feb 2013, 17:55

ያለኢትዮ ቴሌኮም ዕውቅና ውጪ የሚሠራ የሳተላይት መቀበያ በአቶ ጃዋር መኖሪያ ቤት ተገኘ !

Post by sesame » 19 Jul 2020, 05:32

Meles Bisrat
5m ·

ያለኢትዮ ቴሌኮም ዕውቅና ውጪ የሚሠራ የሳተላይት መቀበያ በአቶ ጃዋር መኖሪያ ቤት ተገኘ !

#Ethiopia : ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ ተጠርጥሮ በእስር ላይ በሚገኘውና በቅርቡ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስን (ኦፌኮ) የተቀላቀለው የአቶ ጃዋር መሐመድ መኖሪያ ቤት ሲበረበር፣ ከኢትዮ ቴሌኮም ዕውቅና ውጪ የሚሠራ የሳተላይት መቀበያ መሣሪያ መገኘቱን የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ለፍርድ ቤት አስታውቋል፡፡

መርማሪ ፖሊስ የአቶ ጃዋር ቤት በፍርድ ቤት የብርበራ ፈቃድ ሲበረበር የተለያዩ ሲዲዎች፣ ላፕቶፖች፣ ኮምፒዩተሮች፣ ፍላሾች፣ ኢንተርኔት ለየት ባለ ሁኔታ የሚጠቀሙበት ከኢትዮ ቴሌኮም ውጪ የሆነ የሳተላይት መሣሪያ ተገኝቷል ብሏል፡፡
መርማሪ ቡድኑ እንዳብራራው የድምፃዊው ግድያ ከተፈጸመ በኋላ አቶ ጃዋር ባስተላለፈው ትዕዛዝ በአዲስ አበባ የ14 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱንና ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙን፣ በኦሮሚያ ክልል የወደመውን ንብረት ግምት ገና በመሥራት ላይ ቢሆንም፣ የ167 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱንና በአጠቃላይ የ181 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የሚያረጋግጥ ማስረጃና የሰዎች ምስክርነት ቃል መቀበሉንም ገልጿል፡፡

ብሔርንና ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ አመፅና ዕልቂት እንዲፈጠር ጥሪ መተላለፉንና በርካታ ንብረቶች እንዲወድሙ መደረጉን የገለጸው መርማሪ ቡድኑ፣ ይህንን ድርጊት የሚያረጋግጡለት የ34 ሰዎች የምስክርነት ቃል መቀበሉን፣ 14 የምርመራ ቡድኖች በማዋቀር ከፍተኛ ጉዳት ወደ ተፈጸመባቸው ሻሸመኔ፣ አርሲ ነገሌ፣ ምሥራቅ ሐረርጌና የተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ለምርመራ መላኩን ጠቁሟል፡፡

ኢትዮጵያዊነት ከዘር በላይ ነው!!!

abel qael
Senior Member
Posts: 10765
Joined: 07 May 2007, 03:21
Location: gumamistan

Re: ያለኢትዮ ቴሌኮም ዕውቅና ውጪ የሚሠራ የሳተላይት መቀበያ በአቶ ጃዋር መኖሪያ ቤት ተገኘ !

Post by abel qael » 19 Jul 2020, 06:00

THIS SHOWS HAMASENAY LOOTINESH MERCENARIES ARE PLANTING FAKE INTELLIGENCE INFO AT OMN AND OTHER OROMO OWNED NEWS AND MULTIPURPOSE PROFESSIONAL HEADQUATERS AND HOMES SO AS TO INCRIMINATE EJOLIE LEADERS LIKE JAWAR SO THAT MESHREFET CONCOCTS A PLAUSIBLE-LOOKING LAW SUIT IN ORDER TO IMPRISON THEM FOR LIFE AND EVEN TO KILL THAM. AFTER THE HACALU FIASCO BACKFIRED ON MESHREFET, THEY ARE DESPERATE TO FIND ALTERNATIVE CRIMES TO SLAP ON THE FADINGJAWAR CASE. BUT LITTLE DO HAMASENAY MERCENARIES LIKE MELES BISIRAT OF SHAEBIA EMBASSY IN ADDIS KNOW THAT OROMO WARRIIRS AE ABOUT TO DISMANTLE THE ENTIRE HAMASENAY MERCENARIAL SYSTEM AT GERJI AND TO SURGICALLY REMOVE MESHREFET.


Post Reply