Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Tog Wajale
Member
Posts: 4919
Joined: 23 Dec 2017, 07:23

Breaking News:-- Prosperity Party Will Take Swift Dscisive Military Actions Against Woyane T.P.L.F. Soon If They Declare

Post by Tog Wajale » 15 May 2020, 15:15

የቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት
ይዘት
ኢትዮጵያ
«ትግራይ እንዳለችው ካደረገች እርምጃ ይወሰድባታል»የብልጽግና ፓርቲ
14.05.2020


የትግራይ ክልላዊ መንግስት በተናጥል ምርጫ እንደሚያካሂድ የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ፡፡ የብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሐላፊ አቶ አወሉ አብዲ የትግራይ ክልል መንግስት በክልሉ ምርጫ ማድረግ አይችልም ፤ ካደረገም መንግሥት አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
የትግራይ ክልላዊ መንግስት በተናጥል ምርጫ እንደሚያካሂድ የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ፡፡ ዶክተር ደብረፅዮን ለክልሉ መንግስታዊ መገናኛ ብዙሐን በሰጡት መግለጫ በሀገር ደረጃ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም ተብሎ የሚደመደም ከሆነ ህዝብና የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያሳትፍ ምክክር መደረግ አለበት ብለዋል፡፡ የፌደራሉን መንግስት የሚመራው የብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሐላፊ አቶ አወሉ አብዲ በበኩላቸው የትግራይ ክልል መንግስት በክልሉ ምርጫ ማድረግ አይችልም ፤ ካደረገም መንግሥት አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ታምራት ዲንሳ

አዜብ ታደሰ

DW.COM



Post Reply