Page 1 of 1

DefendTheTruth: ጉራጌኦሮሞች እነዚህ ናቸው!

Posted: 17 Jan 2024, 03:25
by Horus
ደሞ ዱላ አይሸከሙም!


Re: DefendTheTruth: ጉራጌኦሮሞች እነዚህ ናቸው!

Posted: 17 Jan 2024, 03:42
by Misraq
ሶዶ? ማረቆ ነው ክስታኔ?

Re: DefendTheTruth: ጉራጌኦሮሞች እነዚህ ናቸው!

Posted: 17 Jan 2024, 03:51
by Horus
Misraq wrote:
17 Jan 2024, 03:42
ሶዶ? ማረቆ ነው ክስታኔ?
ሶዶ የአገር ስም ነው (ክፍለ አገር እንደ ማለት ነው)፣ እነዚህ የክስታኔ ጉራጌና ኦሮሞ ቅይጦች ናቸው እኛ ላሌጌ እንላቸዋለን ከክስታኔ ሰሜን ስለሆኑ! ላለጌ ማለት ሰሜን ማለት ነው ። እስከ አለምገና ገጃ ያሉት ናቸው ። ማረቆ የኦሮሞ ሳይሆን የሃዲያና መስቃን ጉራጌ ቅይጦች ናቸው ።

ክስታኔኛ ይህ ነው ፤


መስቃንና ክስታኔ ኦልሞስት አንድ ናቸው ፣ እኔ ሙሉ በሙሉ መስቃንኛ እሰማለሁ ፣ ይህ ነው መስቃን ጭፈራው በትንሹ ዝግ ይላል ።

Re: DefendTheTruth: ጉራጌኦሮሞች እነዚህ ናቸው!

Posted: 17 Jan 2024, 04:01
by Selam/
Interesting, never seen something like this before: የለመደኩትን የጉራጌ ወይንም የኦሮሞ የጭፈራና የዘፈን ውህደት ስላላየሁ ፣ በመጀመሪያ የተሰማኝ ስሜት ምን አይነት ‘ጉራማይሌ’ ነው የሚል ነው። አንተስ ለምደኸዋል?
Horus wrote:
17 Jan 2024, 03:25
ደሞ ዱላ አይሸከሙም!


Re: DefendTheTruth: ጉራጌኦሮሞች እነዚህ ናቸው!

Posted: 17 Jan 2024, 04:27
by Horus
Selam/ wrote:
17 Jan 2024, 04:01
Interesting, never seen something like this before: የለመደኩትን የጉራጌ ወይንም የኦሮሞ የጭፈራና የዘፈን ውህደት ስላላየሁ ፣ በመጀመሪያ የተሰማኝ ስሜት ምን አይነት ‘ጉራማይሌ’ ነው የሚል ነው። አንተስ ለምደኸዋል?
Horus wrote:
17 Jan 2024, 03:25
ደሞ ዱላ አይሸከሙም!

ሰምተህ ከሆነ ጭፈራው ብቻ ሳይሆን ሊሪክሱ ላሌ ዬቦላሌ ይላል! ያ የክስታኔኛ ዘፈን አዝማች ነው ። የኤርምያስ ለገሰ ዘመዶች ገጃ አለም ገና ልክ እንደዚህ ነው የሚጨፍሩት ፣ ያንን ነው በመጻፉ የጻፈው ባላገር ዘመዶቼ ጋ ሄጄ ንግግራቸው ኦሮሞኛ ጭፈራቸው ጉራጌኛ ነው ብሏሎ!

አሁን ፈጽሞ ረስተውት ነው እንጂ ገላኖች፣ ያያዎች (የበቾ የማሞ ወልዴ ዘሮች) ሁሉ ሁሉ ግንዳቸው ጉራጌ ነው ። ከዚያም ጨቦን ይዘህ ወንጪን ደንዲ ብለህ ወሊሶ ትገባለህ !!! ብዙዎቹ አሁንም ባህላቸው እንሰትና ቆጮ ነው !!