Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

"ጦርነቱ ቆሞ ሰላም እንዲሰፍን የገላጋይ ቁጥር ከፀበኞች ቁጥር እንዲበልጥ የሰላም ሙቭመንት መጀመር ይኖርብናል። ሰላም ወዳዶች አናሳ ሆነናል።"

Post by sarcasm » 30 Sep 2021, 17:17

አሸናፊ አይኖርም !?

By Abraha Desta


==========
በጦርነቱ ምክንያት የብዙ ወጣቶች ህይወት እየተቀጠፈ ነው። ንብረት እየወደመ ነው። ረሃቡ፣ መፈናቀሉ አለ። የሀገር ኢኮኖሚ እየተሽመደመደ ነው። የዓለም አቀፍ ማሕበረሰብ አጀንዳ ሆነናል። ጦርነቱ ከቀጠለ ችግሮቹ ተባብሰው ይቀጥላሉ። ከቆመ ይቆማሉ።

ሁሉም ወገን ጦርነቱ እንዲቆም ይፈልጋል። የፌደራል መንግስት፣ ህወሓት፣ ተጋሩን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ጦርነቱ እንዲቆም ይፈልጋሉ። ልዩነቱ "እንዴት" ላይ ነው።

የፌደራል መንግስትና ደጋፊዎቹ "ፀረ ኢትዮጵያ" ያሉትን ህወሓትን ቶሎ "አጥፍተው" ጦርነቱ እንዲቆም ይፈልጋሉ። ህወሓትና ደጋፊዎቹ "ፀረ ትግራይ" ያሉዋቸውን ሐይሎችን ቶሎ "ደምስሰው" ጦርነቱ እንዲቆም ይፈልጋሉ። ጠላትን ለማጥፋትና ለመደምሰስ ግዜ እንደሚወስድና ሌሎችን ለማጥፋት ስትሄድ ራስን መጥፋት እንዳለ፣ ሌሎችን ለመደምሰስ ስትመጣ ራስን መደምሰስ እንደሚኖር አይረዱም። ጠላትህ ማጥፋት ስለፈለክ ብቻ አታጠፋውም። ለማሸነፍ ስትነሳ (1) ጦርነቱ ይቀጥላል፤ ችግሩም አብሮ ይቀጥላል። (2) ልትሸነፍም ትችላለህ።

አሁን ምን ሊፈጠር ይችላል?

(1) ፌደራል መንግስት አሸንፎ መቀለ ይገባል?
(2) ህወሓት አሸንፎ አዲስ አበባ ይገባል?
(3) ሁለቱም ይሸነፋሉ? ወይም አይሸናነፉም?
(4) ሁለቱም ያሸንፋሉ፤ ጦርነቱ ተቋርጦ ድርድር ይጀመራል?

(1) የፌደራል መንግስት በጦርነት እንዲያሸንፍ (ሀ) ጦርነቱ ይቀጥላል፤ ጦርነቱ ከቀጠለ ሞቱ፣ ውድመቱ፣ ረሀቡ፣ መፈናቀሉ ይቀጥላል። ይህን ሁሉ ከቀጠለ ምን ማሸነፍ ይባላል? (ለ) መቀለ ገብቶ ማንን ያስተዳድራል? ማንስ ይቀበለዋል? መቀለ እስኪገባ ድረስ የሚኖር እልቂት አስባችሁታል? መከላከያ መቀለ ስለገባ ጦርነቱ ሊቆም ይችላልን? በፍፁም ጦርነት ሊቆም አይችልም!

(2) ህወሓት ቢያሸንፍ (ሀ) እስኪያሸንፍ ስንት ግዜ ጦርነት ያካሂዳል? ጦርነቱ ብዙ ግዜ ይወስዳል። ሞቱ፣ መፈናቀሉ ወዘተ ተባብሶ ይቀጥላል። ህወሓት አዲስ አበባ እስኪደርስ የትግራይ ህዝብ በረሀብ አያልቅም? ህዝብ በረሀብ ካለቀ ጦርነት አሸነፍኩ ይባላል? (ለ) ህወሓት አዲስ አበባ መጥቶስ የአዲስ አበባ ህዝብ ይቀበለዋል? ሰላም ይኖራል? በፍፁም ሰላም አይኖርም!

በመሸናነፍ ሰላም አይኖርም፤ ጦርነቱም አይቆምም።

(3) ሁለቱም ወገኖች ባይሸናነፉስ? ወይም ሁለቱም ቢሸነፉስ?
ሁሉም ተገዳድለው ሐይላቸው ጨርሰው ተዳክመው ቢቆሙስ? ሁለቱም ዓቅማቸው እስኪጨርሱ ድረስ ከተዋጉ (ሀ) ጦርነቱ ብዙ ግዜ ቆየ ማለት አይደል? እናም ብዙ ውድመትና እልቂት ይደርሳል። ብዙ ችግር ከደረሰ መጨረሻ ጦርነቱ ቢቆም ምን ዋጋ አለው? (ለ) ሁለቱም ከተሸነፉ ሀገራችንና ህዝባችን መንግስት አልባ ሆነ ማለት አይደል? እንደ ሀገረ ሶማልያ ሆንን ማለት ኮ ነው።
ጦርነቱ ከቀጠለ አሸናፊ አይኖርም።

(4) ልዩነታቸው በድርድር ለመፍታት ቢስማሙስ? ሁለቱም ወገኖች አሸነፉ ማለት አይደል? ለመደራደር ፍቃደኛ ሆነው ሁለቱም አሸናፊ ቢሆኑ (ሀ) ጦርነቱ ቶሎ ይቆማል። እልቂቱና ውድመቱ ይቆማል። የተፈናቀሉ ወደየቀያቸው ይመለሳሉ፤ የተራቡ ይመገባሉ። ሀገርና ህዝብ ከውድቀት ይድናል። (ለ) ሁለቱም ሲያሸንፉ የጦርነቱ ተሸናፊ ስለማይኖር ከቀጣይ የጦርነት አዙሪት እንወጣለን። አሸናፊው አንድ ሲሆን ሌላኛው ተሸናፊ ይሆናል። ተሸናፊ ካለ በቀጣይ ለበቀል ስለሚዘጋጅ ሌላ ዙር ጦርነት መኖሩ አይቀርም!

ከቀጣይ የጦርነት አዙሪት የሚያስወጣ፣ ሁለቱም አሸናፊ የሚያደርግ እና ጦርነቱን ቶሎ ሚያስቆም እንደውጤቱም ህዝባችንና ሀገራችንን ምናድንበት መንገድ ድርድር ነው። በጦርነቱ የአንድ ወገን አሸናፊ አይኖርም፤ መኖርም የለበትም!

ድርድር አስፈላጊ ቢሆንም ድርድር ስላልን ብቻ ድርድር ሊሳካ ይችላል ወይ? ድርድር እንዲሳካ ቢያንስ ሁለት ነገሮች ያስፈልጉናል።

(1) ሁለቱም ወገኖች ስቶልሜት ወይ ዴድሎክ ደረጃ ላይ መድረስ አለባቸው። መፈታተሽ ይኖርባቸዋል። ሁለቱም ወይ አንዱ "አሸንፋለሁ" የሚል እምነት ካለው ድርድር አይሳካም። ለድርድር እንዲቀርቡ ሁለቱም ተመጣጣኝ ዓቅም ሊኖራቸው ይገባል። አሸንፋለሁ ብቻ ሳይሆን ልሸነፍ እችላለሁ ም ብለው የሚያስቡበት ደረጃ መድረስ አለባቸው። አስታውሱ፦ በግ እና አንበሳ ሊደራደሩ አይችሉም።
አሁን ዴድሎክ ላይ ናቸው ብዬ አስባለሁ። ስለዚህ የማደራደር ዕድሉ አሁን ነው። መከላከያ መቀለ ከገባ ወይም ህወሓት ወደ አዲስ አበባ ከመረሸ ድርድሩ አይሳካም ወይም ጤናማ ድርድር አይሆነም።

(2) ሁለቱም ወገኖች ዴድሎክ አጋጥሟቸውም የቲፎዞ ነገር ካለ ድርድሩ ላይሳካ ይችላል። ሁለት ሰዎች ተጣልተው እየተደባደቡ ሳለ ገላጋይ ገብቶ ሊለያያቸውና ሊሸመግላቸው ወይ ሊያስታርቃቸው ይችላል። ፀቡ በሁለቱም ወገን ብዙ ሰው (ቲፎዞ) ያካተተ ከሆነና ገላጋዮቹ ከፀበኞቹ ያነሰ ቁጥር ቢኖራቸውስ? ጭራሽ ሰላም ወዳድ ገላጋዮቹ እንደ "መሃል ሠፋሪ" ቢታዩና ባይሳካስ? ከፀቦኞቹ ጎን የተሰለፈ ብዙ አጨብጫቢ ቲፎዞ ቢኖርስ? ፀበኞቹ ዴድሎክ ላይ ሆኖውም በአጨብጫቢዎች ቅስቀሳ ሼም ይዟቸው ህይወታቸው እስኪያልፍ ሊደባደቡ ይችላሉ።

ስዚህ ጦርነቱ ቆሞ ሰላም እንዲሰፍን የገላጋይ ቁጥር ከፀበኞች ቁጥር እንዲበልጥ የሰላም ሙቭመንት መጀመር ይኖርብናል። ሰላም ወዳዶች አናሳ ሆነናል።

ሁለቱም ወገኖች አሸናፊ የሚሆኑበት የድርድር መንገድ እንዲከተሉ ግፊት እናድርግ!
ሰላም!
Please wait, video is loading...

sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

Re: "ጦርነቱ ቆሞ ሰላም እንዲሰፍን የገላጋይ ቁጥር ከፀበኞች ቁጥር እንዲበልጥ የሰላም ሙቭመንት መጀመር ይኖርብናል። ሰላም ወዳዶች አናሳ ሆነናል።"

Post by sarcasm » 07 Oct 2021, 05:48

When he started talking about Peace Movement, Abiy ahmed's regime has put put Abraha Desta in jail.

Ethiopia detains former official from Tigray interim government

NAIROBI, Oct 2 (Reuters) - A former senior official in an interim government for Ethiopia's Tigray region appeared in court on Saturday over allegations of inciting conflict between the Tigrayan people and the central government, and possessing an illegal gun, his lawyer said.

War erupted in Nov. 2020 in the northern region of Tigray between the federal government and forces aligned with the region's ruling party, the Tigray People's Liberation Front (TPLF). Soon after, the federal government seized the Tigray capital and appointed an interim administration for Tigray.

Abraha Desta served in that federally-appointed administration as the head of the Bureau of Social Affairs of Tigray. He was previously a member of Tigrayan opposition party Arena, which resisted the TPLF, and had spent three years in jail under the former TPLF-led government. He is the highest-ranking official from the interim administration to be arrested.

Abraha held his position until late June, when Tigrayan forces retook most of Tigray and he left for the Ethiopian capital Addis Ababa.

He was arrested there on Thursday, one day after writing an open letter to Addis Ababa's new mayor on Facebook denouncing what he alleged were arbitrary arrests of ethnic Tigrayans and mounting discrimination.

A Reuters investigation earlier this year found that Ethiopian police had arrested hundreds of ethnic Tigrayans in Addis Ababa without charge. Police denied at the time that suspects were being targeted over their ethnicity. read more

On Saturday, Abraha was remanded for nine days, said his lawyer, who requested Reuters not publish his name.



Continue reading https://www.reuters.com/world/africa/et ... 021-10-02/

Post Reply