Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 44306
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » Yesterday, 11:20
መርካቶ ሜዳ ጭቃ ሆና አድጌባታለሁ!
የመጀመሪያው የገበያ አዳላሽ ተሰርቶ እነ አቤ ጉበኛውን ተገናኝቼበታለሁ!
እነ መሃመድ ሳላ በራድና ፉል በልቼበታለሁ
እነ ሲሊማ አዲስ ከተማ የካውቦይ ፊልም አይቼበታለሁ
መካቶ የዛሬን 1/10ኛ ስፋት ሆና አውቃታለሁ
የዛሬ አመዴ ለማ አትክልት ተራና የጠ/ግዛት አቶቢስ የነ ማሞ ካቻ ፈጣን ማመላለሻ መናሃሪያ ሆና ተሳፍሬባታለሁ!
መርካቶ ለማያውቃትና ውጭ ለቆመ አንድ ግዙፍ ቀውስና ትርምስ ነች!
ውስጧ ግ ን አስገራሚ ስርዓት ፣ አስገራሚ ድርጅት ፣ አስገራሚ ሲስተም ነች!
ለዚህ የመጨረሻ ምስክሩ አፈራረሷ ነው!
ተመልከቱ ! መርካቶ ዝም ብላ በቡልዶዘር አትደረመስም ! አትደመሰስም!
ተመልከቱ እያንዳንዱ እንጨት ፣ እያንዳንዱ ድንዳይ ፣ እያንዳንዱ ቆርቆሮና ምስማር በስርዓት ተነቆሎ ሲሰበሰብ ከጎኑ ገበያው አላንዳች ያ ሆያ ሆዬ ስራውን ያካሂዳል!
መርካቶ ማለት ያ ነው! ሚሊዮን ሰው እያንዳንዱ የራሱን ስራ በስርዓት የሚቀውጥበት የሲስተሞች ሁሉ ሲስተም!
MERKATO - THE MOTHER OF ALL ORDERS !!!
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 44306
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » Yesterday, 11:33
ገበያው ይጦፋል! በጎኑ ፈረሳው ይጦፋል! መርካቶ ለደቂቃ እንኳን ስራ ማይፈታባት የትጉሃኖቹ ምድር!!! እጹብ ድንቅ!!!!
ልብ በሉ ይህ ሰፈር በሙሉ አጼ ምኒልክ አዲሳባን ሲያቀኑ ይህ ዙሪያው ሁሉ ዘንዶ ሁሉ የሚበዛበት ጫካ ነበር! ፊታውራሪ ሃብተ ጎርዲስ ዲነግዴ የመጀመሪያ ግዙፍ የሳር ቤት እልፍኝ ዛሬ ራጉኤልና አንዋር መስጂድ የተሰራበት ግቢ ነበር ። ቅጠል ተራ ማለት ድሮ ሃብተ ጎርጊስ ድልድይ የሚባለው ወንዝና ቦታ ነው ።
አሜሪካ በ1903 አካባቢ ከምኒልክ ጋር ዲፕልማሲ ስትጀምር ለቆንስላ የሚሆን ትልቅ ቤትና ግቢ ባዲሳባ ስላልነበረ ሃብተ ጎርጊስ ቤታቸው ያሜሪካ ቆንስላ እንዲሆን ሰጥተው እርሳቸው ወደ 4 ኪሎ ግቢ ሄዱ ! መርካቶ መላው የሃብቴ ዲነግዴ ርስት ነበር ።
በዚያን ዘመን የፍታራሪ ሃብቴ ግቢ ይባል የነበረው የአሜሪካን ግቢ ተብሎ ዛሬ ድረስ ያ ሰፈር አሜሪካን ግቢ ይባላል!
-
Horus
- Senior Member+
- Posts: 44306
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Post
by Horus » Today, 12:33
ቱስ ቱስ ቲያጎ!
ዛሬ ላይ ጉራጌኮ ያለው ቦሌ ፒያሳ ቤተልና ሃያት ሽሮ ሜዳ ሰሜን ምስዘጋጃ ነው! ላንቺ ዘመዶች ለጀማሪዎቹ አስተላለፍነውኮ ገና ድሮ! እርግጥ ፎቆቹ የኛ ናቸው ! ጉራጌ ሲባል የመጀመሪያ ትውልድ ይነግዳል ፣ ሁለተኛው ትውልድ ፍብሪካ ይከፍታል ወይም ፕሮፌሰር ነው! አለቀ!
-
Tiago
- Member
- Posts: 3549
- Joined: 30 Jul 2018, 02:09
Post
by Tiago » 12 minutes ago
ዛሬ ላይ ጉራጌኮ ያለው ቦሌ ፒያሳ ቤተልና ሃያት ሽሮ ሜዳ ሰሜን ምስዘጋጃ ነው! ላንቺ ዘመዶች ለጀማሪዎቹ አስተላለፍነውኮ ገና ድሮ! እርግጥ ፎቆቹ የኛ ናቸው ! ጉራጌ ሲባል የመጀመሪያ ትውልድ ይነግዳል ፣ ሁለተኛው ትውልድ ፍብሪካ ይከፍታል ወይም ፕሮፌሰር ነው! አለቀ!
ኦሮሞ ሊሰለቅጣት ተዘጋጅቷል
ቦሌ ፒያሳ ቤተልና ሃያት ሽሮ ሜዳ ሰሜን ምስዘጋጃ Who is / was living in these places apart from WooraGay?? who were the pioneers? who established TMS ,hospitals,telecommunication,etc?
wooraGays ?:lol:
unless you are deliberately refraining from commenting on the current Oromo demand on owning Addis Ababa, out of fear or you are one of those sick ethnocentric individuals.