Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum

Horus
Senior Member+
Posts: 40166
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: NEW- የኮቪድ ወረርሽኝ እስኪወገድና ቀጣዩ ምርጫ እስከሚካሔድ የብልጽግና ፓርቲ ሐገር የማስተዳደር ኃላፊነት አለበት።- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሰጡት መ

Post by Horus » 07 May 2020, 03:26

ሚኒሊክ
ያቢይ ስህተት ምን እንደ ሆነ ልንገርህ ። ያቢይ ችግር ወያኔ፣ ጃዋር፣ ልደቱ ፣ አራርሶ አይደሉም። ያቢይ ችግር ራሱ አቢይ ነው ። ከመስክረም በኋላ እስከ ተፈለገ ድረስ ምርጫ ማራዘም ይቻላል ። እነሱ የጻፉት ሕገ መንግስት ተቢዬ ራሳቸው ሊለውጡት ይችላሉ ፣ ግን እህ እንዲሆን አቢይ ለ1፣ 2፣ ወይ 3 አመት ከሌሎች ፓርቲዎች ወይ ሊሂቃን ጋር ስልጣን መጋራት መሻማት አለበት ። ይህ ግድ ነው ። ይህን እምቢ እያለ ማንም አያምነውም ። አቢይኮ እግዚአብሄር አይደለምን ። ራሱ ስልጣን የሚወድ የፖለቲካ እንሰሳ ነው በቃ !!! ዝሆኑን በስሙ ጥሩት፣ ያኔ ሁሉ ነገር ግልጽ ይሆናል !! አሚን !!!!

MINILIK SALSAWI
Senior Member
Posts: 11060
Joined: 24 Aug 2012, 12:02
Contact:

Re: NEW- የኮቪድ ወረርሽኝ እስኪወገድና ቀጣዩ ምርጫ እስከሚካሔድ የብልጽግና ፓርቲ ሐገር የማስተዳደር ኃላፊነት አለበት።- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሰጡት መ

Post by MINILIK SALSAWI » 07 May 2020, 04:59

Horus wrote:
07 May 2020, 03:26
ሚኒሊክ
ያቢይ ስህተት ምን እንደ ሆነ ልንገርህ ። ያቢይ ችግር ወያኔ፣ ጃዋር፣ ልደቱ ፣ አራርሶ አይደሉም። ያቢይ ችግር ራሱ አቢይ ነው ። ከመስክረም በኋላ እስከ ተፈለገ ድረስ ምርጫ ማራዘም ይቻላል ። እነሱ የጻፉት ሕገ መንግስት ተቢዬ ራሳቸው ሊለውጡት ይችላሉ ፣ ግን እህ እንዲሆን አቢይ ለ1፣ 2፣ ወይ 3 አመት ከሌሎች ፓርቲዎች ወይ ሊሂቃን ጋር ስልጣን መጋራት መሻማት አለበት ። ይህ ግድ ነው ። ይህን እምቢ እያለ ማንም አያምነውም ። አቢይኮ እግዚአብሄር አይደለምን ። ራሱ ስልጣን የሚወድ የፖለቲካ እንሰሳ ነው በቃ !!! ዝሆኑን በስሙ ጥሩት፣ ያኔ ሁሉ ነገር ግልጽ ይሆናል !! አሚን !!!!
ይህ በኢሕአዴግ/ብልጽግና ሰፈር እኮ የማይታሰብ ነው። ሕጉን በፈለጉት ስታይል አሽከርክረው ወደፊት ይመጣሉ እንጂ ሕገመንግስትም ይተርጎም ያሉትን በፈለጉት ስታይል ተርጉመው ያመጡታል እንጂ በፍጹም ስልጣን ከኢሕአዴግ/ብልጽግና ሰፈር እንዲወጣ አይፈለግም። ምናልባት ሰሞኑን በመግለጫቸው የሕገመንግስት ትርጓሜውን የደገፉ ፓርቲዎችን ሊያስጠጋቸው ይችላል። ካሁን ቀደምም ሕገመንግስቱን በመመሪያና በቀላጤ ሲሽሩ ነበር ለነሱ አዲስ ነገር አይደለም።

MINILIK SALSAWI
Senior Member
Posts: 11060
Joined: 24 Aug 2012, 12:02
Contact:

Re: NEW- የኮቪድ ወረርሽኝ እስኪወገድና ቀጣዩ ምርጫ እስከሚካሔድ የብልጽግና ፓርቲ ሐገር የማስተዳደር ኃላፊነት አለበት።- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሰጡት መ

Post by MINILIK SALSAWI » 07 May 2020, 06:02

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከህጋዊ መንገድ ውጪ ስልጣን ለመያዝ የሚንቀሳቀሱ ናቸው ያሏቸውን የፖለቲካ ፓርቲዎችና ፖለቲከኞች አስጠነቀቁ፡፡መንግስታቸው በህገ መንግስቱና በህገ መንግስታዊ ሥርዓቱ ካልሆነ በስተቀር የጨረባ ምርጫ ለማድረግ በሚነሱት ላይ ወሳኝ እርምጃ ለመውሰድ ይገደዳል ብለዋል፡፡ ለዚህም መንግስታቸው ዝግጁ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ስልጣንን ያለ ምርጫና ከህግ ውጪ በሁከትና በብጥብጥ ካልሰጣችሁን ሀገር አተራምሳለሁ የሚለውን ማንኛውንም ሀይል አንታገስም ብለዋል፡፡

MINILIK SALSAWI
Senior Member
Posts: 11060
Joined: 24 Aug 2012, 12:02
Contact:

Re: ስልጣንን ያለ ምርጫና ከህግ ውጪ በሁከትና በብጥብጥ ካልሰጣችሁን ሀገር አተራምሳለሁ የሚለውን ማንኛውንም ሀይል አንታገስም – ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ

Post by MINILIK SALSAWI » 07 May 2020, 08:19

ምርጫው እስኪካሄድ ድረስ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት መቆየትና የሽግግር ሂደቱን መምራት የተሻለ ነው ብለን እናምናለን – አብን

Read Full press statement - https://mereja.com/amharic/v2/266952


Post Reply