Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Selam/
Senior Member
Posts: 17804
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

ኢትዮጵያ ውስጥ ልዩነቶችን የሚያስተናግድ የፖለቲካ መሰረት አለ ብሎ የሚያስብ ሰው አጭበርባሪ ወይንም ድፍን ነው!

Post by Selam/ » 21 Apr 2026, 22:41

አሁን ሃገራችን ውስጥ ያለው የፖለቲካ ባህል ተቸርችፎ ተከርክሞ፣ የጎጥ ማንነት መገለጫና የገንዘብ ማከማቻ፣ የሎሌዎች ማጠራቀሚያና ያፈነገጠውን የመኮርኮሚያ መሳሪያ ሆኖል እንጂ የርዕዮተ ዓለም መፎካከሪያና የሃሳብ መፋጫ አይደለም።

ባለ ጊዜዎቹ ህጉን ለስልጣናቸው እንዲመቻቸው አድርገው ይለጥጡታል፣ የቀነጭቡታል ወይንም ይደፈጥጡታል እንጂ ተፎካካሪዎችንም ይሁን ህዝቡን የሚያሳትፍና ቅራኔን ሊያጠፋ የሚችልን የህግ ማሻሻያ ለማድረግ በፍፁም ፍላጎት አያሳዩም። በዚህም ምክንያት በተለይ ወጣቱ መብቱን እንዳይረዳና ከፖለቲካ ተሳትፎ እንዲሸሽ አድርገውታል።

ህዝብ እየተሸማቀቀና ሚዛናዊ የፖለቲካ ባህል ሳይዳብር፣ ብልጭልጭ መንገድ ብቻ ዘላቂ ለውጥና ዕድገት ያስገኛል ብሎ ማሰብ ራስን ማታለል ነው።


Selam/
Senior Member
Posts: 17804
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ኢትዮጵያ ውስጥ ልዩነቶችን የሚያስተናግድ የፖለቲካ መሰረት አለ ብሎ የሚያስብ ሰው አጭበርባሪ ወይንም ድፍን ነው!

Post by Selam/ » 22 Apr 2026, 03:16

ምን እንድልልህ ፈልገህ ነው?

የዛሬውን የቂም በቀል ፖለትካ መሠረት የጣለችው እኮ ያንተዋ ስስታሟ TPLF ነች። ለራሳችሁ የፖለቲካ ብዝሃነትን ሳታስተናግዱና ለውጥ ሳታመጡ ባላችሁበት ቦታ ተቀርቅራችሁ ቀርታችሁ፣ ከተከዜ
አልፎ የሚሄድ የፖለቲካ ተፅዕኖ አድርጋለሁ ማለት ትርፉ ጉልበትን ማዛልና መገጣጠብ ነው።

Post Reply